HadeethEnc · 1.23.0
የሚያሳልፉት ቤተሰባቸውን በማገልገል ነው። ሶላት ሲደርስ ሶላት ለመስገድ ይወጣሉ።" አለች።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአስወድ ቢን የዚድ እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «ዓኢሻን ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ቤት ውስጥ ስለሚሰሩት ስራ ጠየቅኳት? እርሷም: "የሚያሳልፉት ቤተሰባቸውን በማገልገል ነው። ሶላት ሲደርስ ሶላት ለመስገድ ይወጣሉ።" አለች።»
02
Explanation
የአማኞች እናት ዓኢሻ -አላህ መልካም ስራዋን ይውደድላትና - ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ቤታቸው ውስጥ ስለነበራቸው ሁኔታ ተጠየቁ። ጊዜያቸውን እንዴት ነበር ያሳልፉ ይሰሩ የነበሩት? እርሷም: እንደማንኛውም ሰው እርሳቸውም ሰው ነበሩ። ወንዶች ቤት ውስጥ ይሰሩ የነበሩትን ይሰሩ ነበር። ራሳቸውንና ቤተሰባቸውን ያገለግሉ ነበር። ፍየላቸውን ያልባሉ፣ ልብሳቸውን ይሰፋሉ፣ ጫማቸውን ይጠግናሉ፣ የተቀደደ ባልዲያቸውን ይለጥፋሉ። ሶላት ኢቃም የሚልበት ወቅት ላይ ሲደርሱ ምንም ሳያዘገዩ ወደርሷ ይወጣሉ በማለት መለሰች።
03
Benefits
ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- የነበራቸውን የተሟላ መተናነስና ለቤተሰባቸው የነበራቸውን በጎነት እንረዳለን።
ዱንያዊ ስራዎች ባሪያዎችን ከሶላት ሊያዘናጓቸው እንደማይገባ እንረዳለን።
ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሶላትን በመጀመሪያ ወቅት ላይ በመስገድ እንደዘወተሩ እንረዳለን።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ከዚህ ሐዲሥ በመተናነስ ላይ፣ ኩራትን በመተውና ሰውዬው ቤተሰቡን እንዲያገለግል መነሳሳቱን እንረዳለን።"
ዱንያዊ ስራዎች ባሪያዎችን ከሶላት ሊያዘናጓቸው እንደማይገባ እንረዳለን።
ነቢዩ -የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሶላትን በመጀመሪያ ወቅት ላይ በመስገድ እንደዘወተሩ እንረዳለን።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ከዚህ ሐዲሥ በመተናነስ ላይ፣ ኩራትን በመተውና ሰውዬው ቤተሰቡን እንዲያገለግል መነሳሳቱን እንረዳለን።"
Attribution
[ቡኻሪ ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

