HadeethEnc · 1.23.0
'ልታሟሉት ከሚገቡ መስፈርቶች ሁሉ ልታሟሉት እጅግ የተገባው ብልትን ሐላል ያደረጋቹበትን መስፈርት ነው።'
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከዑቅበህ ቢን ዓሚር -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ: 'ልታሟሉት ከሚገቡ መስፈርቶች ሁሉ ልታሟሉት እጅግ የተገባው ብልትን ሐላል ያደረጋቹበትን መስፈርት ነው።'"
02
Explanation
ነቢዩ ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም መሙላቱ እጅግ የተገባው መስፈርት በሴት መጠቀምን ሐላል ለማድረግ ሰበብ የሆነውን መስፈርት መሆኑን እየነገሩን ነው። ይህም ሚስት በጋብቻው ውል ወቅት የምታስቀምጣቸው የተፈቀዱ መስፈርቶች ናቸው።
03
Benefits
ሐላልን ሐራም ሐራምን ሐላል ከሚያደርጉ መስፈርቶች በስተቀር ከሁለቱ ጥንዶች መካከል አንዱ ለሌላው ቃል የገባውን መስፈርቶች መሙላት ግዴታ ነው።
የኒካሕን መስፈርቶች ማሟላት ከሌላ መስፈርቶች የበለጠ ሊሟላ የሚገባው ነው። ምክንያቱም እነዚህ መስፈርቶች ብልትን ሐላል ለማድረግ የሚገቡት ቃል ነውና።
ኢስላም የጋብቻ መስፈርቶችን እንዲጠበቁ አፅንኦት መስጠቱ ጋብቻ በኢስላም ውስጥ ያለው ደረጃ ከፍ ያለ መሆኑን ያስረዳል።
የኒካሕን መስፈርቶች ማሟላት ከሌላ መስፈርቶች የበለጠ ሊሟላ የሚገባው ነው። ምክንያቱም እነዚህ መስፈርቶች ብልትን ሐላል ለማድረግ የሚገቡት ቃል ነውና።
ኢስላም የጋብቻ መስፈርቶችን እንዲጠበቁ አፅንኦት መስጠቱ ጋብቻ በኢስላም ውስጥ ያለው ደረጃ ከፍ ያለ መሆኑን ያስረዳል።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

