HadeethEnc · 1.23.0
ብርቱ የሚባለው ታግሎ ያሸነፈ ሳይሆን በቁጣ ወቅት እራሱን የተቆጣጠረ ነው።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና-እንደተላለፈው የአላህ መልክተኛ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም እንዲህ ብለዋል፡ "ብርቱ የሚባለው ታግሎ ያሸነፈ ሳይሆን በቁጣ ወቅት እራሱን የተቆጣጠረ ነው።"
02
Explanation
ነቢዩ ሰለላሁ ዐለይሂ ወሰለም ትክክለኛ ሀይል አካላዊ ሀይል ወይም ጉልበተኞችን የሚጥል ሳይሆን ብርቱና ሀይለኛ የሚባለው ቁጣው በሚበረታ ወቅት ነፍሱን የታገለና ያሸነፋት መሆኑን ገለፁ። ምክንያቱም ይህ ሰው ነፍሱን የመቆጣጠርና ሰይጣንን የማሸነፍ አቅም እንዳለው ይጠቁማልና።
03
Benefits
የቻይነትና ነፍስን በቁጣ ወቅት የመቆጣጠር ትሩፋትን እንረዳለን። ይህ ኢስላም ያነሳሳበት ከሆኑ መልካም ስራዎች መካከል አንዱ ነውና።
ነፍስን በቁጣ ወቅት መታገል ጠላትን ከመታገልም የበለጠ ከባድ መሆኑን እንረዳለን።
ጃሂሊዮች ለሀይለኝነት የሰጡትን ትርጓሜ ኢስላም ወደ ክቡር መገለጫ ስነ ምግባር መለወጡን እንረዳለን። ከሰዎች ሁሉ እጅግ ብርቱ የነፍሱን ልጓም የተቆጣጠረ ነውና።
በግለሰብም ደረጃ ይሁን በማህበረሰብ ደረጃ ጉዳት ከማስከተሉ አኳያ ከቁጣ መራቅ እንደሚገባ እንረዳለን።
ነፍስን በቁጣ ወቅት መታገል ጠላትን ከመታገልም የበለጠ ከባድ መሆኑን እንረዳለን።
ጃሂሊዮች ለሀይለኝነት የሰጡትን ትርጓሜ ኢስላም ወደ ክቡር መገለጫ ስነ ምግባር መለወጡን እንረዳለን። ከሰዎች ሁሉ እጅግ ብርቱ የነፍሱን ልጓም የተቆጣጠረ ነውና።
በግለሰብም ደረጃ ይሁን በማህበረሰብ ደረጃ ጉዳት ከማስከተሉ አኳያ ከቁጣ መራቅ እንደሚገባ እንረዳለን።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

