እንዳትገድለው! ከገደልከው እርሱ ከመግደልህ በፊት የነበርክበት ደረጃ ላይ ይሆንና አንተ ደሞ የተናገረውን ንግግር ከመናገሩ በፊት በነበረው ደረጃ ላይ ትሆናለህ።" አሉ።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከሚቅዳድ ቢን ዐምር አልኪንዲይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: እርሱ ለአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዲህ አላቸው: «ከከሀዲዎች መካከል ከአንዱ ጋር ብንገናኝና ብንጋደል አንድ እጄንም በሰይፉ መቶ ቢቆርጣት ከዚያም ከኔ ለማምለጥ ወደ ዛፍ ተጠግቶ ለአላህ ብዬ እስልምናን ተቀብያለሁ ቢል የአላህ መልክተኛ ሆይ! ንገሩኝ እስኪ ይህን ከተናገረ በኋላ ልግደለውን? የአላህ መልክተኛም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና "እንዳትገድለው።" አሉ። እርሱም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! አንድ እጄን‘ኮ ቆርጧል። ከዚያም እጄን ከቆረጣት በኋላ ነው ይህቺን የተናገራት!" አለ። የአላህ መልክተኛም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና "እንዳትገድለው! ከገደልከው እርሱ ከመግደልህ በፊት የነበርክበት ደረጃ ላይ ይሆንና አንተ ደሞ የተናገረውን ንግግር ከመናገሩ በፊት በነበረው ደረጃ ላይ ትሆናለህ።" አሉ።»
Explanation
ነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንዳትገድለው! አሉት።
እርሱም: የአላህ መልክተኛ ሆይ! እርሱ’ኮ አንድ እጄን ቆርጧል። ይህን ከማድረጉም ጋር አልገድለውምን? አላቸው።
ነቢዩም (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና: እንዳትገድለው! እርሱ ደሙን ማፍሰስ ከተከለከሉት ሆኗል። ከሰለመ በኋላ ከገደልከው እርሱ በእስልምናው ደሙ የተጠበቀ ስለሆነ ባንተ ደረጃ ይሆንና አንተ ደሞ እርሱን በመግደልህ በቂሷስ ህግ መሰረት ደምህ መፍሰሱ የተፈቀደ ስለምትሆን በርሱ ደረጃ ላይ ትሆናለህ! አሉት።
Benefits
ከከሃዲዎች መካከል አንዱ በጦርነት መሀል ከሰለመ እስልምናን የሚቃረን ነገር በግልፅ እስካልታየበት ድረስ ደሙ የተጠበቀና እርሱን ከመጉዳት መቆጠብም ግዴታ ይሆናል።
አንድ ሙስሊም ዝንባሌው ለወገንተኝነትና ለበቀል ሳይሆን ሸሪዓን የተከተለ መሆኑ ግዴታ ነው።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «ይህ ታሪክ አልተከሰተም የሚለው ሚዛን ይደፋል በሚለው አቋም ላይ ተመስርተን ድንገታዊ ክስተቶች ከመከሰታቸውም በፊት (ያላቸውን ኢስላማዊ ፍርድ) መጠየቁ ይፈቀዳል የሚልን እንረዳለን። ከአንዳንድ ሰለፎች ሳይከሰት መጠየቅ እንደሚጠላ የተዘገበው መከሰቱ ያልተለመደ የሆኑ ጉዳዮችን በሚል ይተረጎማል። በተለምዶ ሊከሰቱ የሚመቹ ጉዳዮችን ለማወቅ መጠየቅ ግን የተደነገገ ነው።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

