HadeethEnc · 1.23.0
ዒድን ከዑመር ቢን ኸጧብ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ጋር ለመስገድ ተገኘሁ። እንዲህም አሉ: "እነዚህ ሁለት ቀናቶች የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ከመጾም የከለከሉት ቀናቶች ናቸው። (እነርሱም) ከጾማችሁ የምትፈቱበት ቀን (ዒድ አልፊጥር) እና ሌላኛው ቀን ደግሞ ከእርዳችሁ የምትበሉበት የሆነው ቀን (ዒደል አድሓ) ናቸው።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ኢብኑ አዝሃር ነፃ ያወጡት ባሪያ ከሆነው ከአቡ ዑበይድ እንደተላለፈው እንዲህ አለ: «ዒድን ከዑመር ቢን ኸጧብ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ጋር ለመስገድ ተገኘሁ። እንዲህም አሉ: "እነዚህ ሁለት ቀናቶች የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ከመጾም የከለከሉት ቀናቶች ናቸው። (እነርሱም) ከጾማችሁ የምትፈቱበት ቀን (ዒድ አልፊጥር) እና ሌላኛው ቀን ደግሞ ከእርዳችሁ የምትበሉበት የሆነው ቀን (ዒደል አድሓ) ናቸው።"»
02
Explanation
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ዒደል ፊጥርና ዒደል አድሓን ከመጾም ከለከሉ። ዒደል ፊጥር ከረመዳን ወር ጾም የሚፈታበት ቀን ስለሆነ ነው። የዒደል አድሓ ቀን ደግሞ ከኡድሒያው ስጋ የሚበላበት ቀን ስለሆነ ነው።
03
Benefits
የዒደል ፊጥርና አድሓ ቀናትን መጾም ክልክል ነው። እንዲሁም የአያመ ተሽሪቅ ቀናትም ዒደል አድሓን ተከትለው የሚመጡ ቀናት ስለሆኑ ሐጅ ላይ ሆኖ የሚያርደውን ያላገኘ ሰው እስካልሆነ ድረስ መጾም ክልክል ነው። ሐጅ ላይ የሚያርደው ያጣ ግን ለርሱ አያመ ተሽሪቆችን መጾም ይፈቀድለታል።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «ሁለቱ ቀናት ባህሪያቸውን ገልፆ የመከልከሉ አስፈላጊነት ማፍጠር ግዴታ የሆነበትን ምክንያት ለመጠቆም ነው ተብሏል። እርሱም በዒደል ፊጥር ከጾም መለያየታችንንና ከዚህ ቀን በኋላ ያለውን ቀን በመብላት ጾሙ መሙላቱን ለማሳየት ሲሆን ዒደል አድሓ ደግሞ በማረድ ቁርባን ያቀረበ ሰው ካረደው እንዲበላ ነው።»
ኹጥባ አድራጊ ሰው በኹጥባው ወቅት ከጊዜው ጋር ተያያዥ የሆኑን ህግጋት ማውሳትና አጋጣሚዎችን ማጥናቱ ይወደድለታል።
ከኡዱሒያ እርድ መብላት በሸሪዓ የተደነገገ መሆኑን እንረዳለን።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «ሁለቱ ቀናት ባህሪያቸውን ገልፆ የመከልከሉ አስፈላጊነት ማፍጠር ግዴታ የሆነበትን ምክንያት ለመጠቆም ነው ተብሏል። እርሱም በዒደል ፊጥር ከጾም መለያየታችንንና ከዚህ ቀን በኋላ ያለውን ቀን በመብላት ጾሙ መሙላቱን ለማሳየት ሲሆን ዒደል አድሓ ደግሞ በማረድ ቁርባን ያቀረበ ሰው ካረደው እንዲበላ ነው።»
ኹጥባ አድራጊ ሰው በኹጥባው ወቅት ከጊዜው ጋር ተያያዥ የሆኑን ህግጋት ማውሳትና አጋጣሚዎችን ማጥናቱ ይወደድለታል።
ከኡዱሒያ እርድ መብላት በሸሪዓ የተደነገገ መሆኑን እንረዳለን።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

