HadeethEnc · 1.23.0
ጾመኛ መሆኑን ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ሰው ጾሙን ይሙላ። ያበላውና ያጠጣው አላህ ነውና።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ሁረይራ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ብለዋል: "ጾመኛ መሆኑን ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ሰው ጾሙን ይሙላ። ያበላውና ያጠጣው አላህ ነውና።"»
02
Explanation
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) የግዴታ ጾም ወይም የሱና ጾም ፁሞ ጾመኛ መሆኑን ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ሰው ጾሙን ይሙላ እንዳያፈጥር ብለው ገለፁ። ምክንያቱም ማፍጠርን አስቦ ሳይሆን ይህ (በመርሳቱ ምክንያት) አላህ የሰጠው ያበላው ያጠጣው ሲሳይ ነውና።
03
Benefits
ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ሰው ጾሙ ትክክለኛ መሆኑን እንረዳለን።
ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ሰው በምርጫው ስላልሆነ መብላቱ ጥፋተኛ አያደርገውም።
አላህ ለባሮቹ ያለውን እዝነትና ለነረሱ ማቅለሉን፣ ጭንቅና ችግርንም ከነርሱ ላይ ማንሳቱን ተረድተናል።
አንድ ጾመኛ ሶስት መስፈርቶች የተሟሉ ጊዜ ካልሆነ በቀር ጾሙን አይፈታም። አንደኛ: አውቆ መሆኑ ነው፤ የማያውቅ ከሆነ አይፈታም። ሁለተኛ: እያስታወሰ መሆን አለበት። ረስቶ ከሆነ የበላው ጾሙም ትክክለኛ ነው። (ሲያስታውስ እስከታቀበ ድረስ) በርሱም ላይ ምንም ቀዿእ አይኖርበትም። ሶስተኛ: ፈቅዶ መሆን አለበት። ተገዶ መሆን የለበትም። በምርጫው የሚያስፈታ ነገር መውሰድ አለበት።
ረስቶ የበላ ወይም የጠጣ ሰው በምርጫው ስላልሆነ መብላቱ ጥፋተኛ አያደርገውም።
አላህ ለባሮቹ ያለውን እዝነትና ለነረሱ ማቅለሉን፣ ጭንቅና ችግርንም ከነርሱ ላይ ማንሳቱን ተረድተናል።
አንድ ጾመኛ ሶስት መስፈርቶች የተሟሉ ጊዜ ካልሆነ በቀር ጾሙን አይፈታም። አንደኛ: አውቆ መሆኑ ነው፤ የማያውቅ ከሆነ አይፈታም። ሁለተኛ: እያስታወሰ መሆን አለበት። ረስቶ ከሆነ የበላው ጾሙም ትክክለኛ ነው። (ሲያስታውስ እስከታቀበ ድረስ) በርሱም ላይ ምንም ቀዿእ አይኖርበትም። ሶስተኛ: ፈቅዶ መሆን አለበት። ተገዶ መሆን የለበትም። በምርጫው የሚያስፈታ ነገር መውሰድ አለበት።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

