HadeethEnc · 1.23.0
ሰሑር ተመገቡ! በሰሑር ውስጥ በረከት አለ።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአነስ ቢን ማሊክ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ብለዋል: "ሰሑር ተመገቡ! በሰሑር ውስጥ በረከት አለ።"»
02
Explanation
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በሰሑር ጉዳይ አነሳሱ። እርሱም ለጾም ዝግጅት ሌሊቱ መጨረሻ ላይ መመገብ ነው። በሌሊቱ መጨረሻ ወቅት ለሰሑርና ለዱዓእ መቆም (በረከት) - ማለትም ብዙ ምንዳና አጅር - ያስገኛል። ለጾም ያነቃቃል፤ ክብደቱንም ያቀላል።
03
Benefits
ሰሑር መብላትና ሸሪዓዊ ትእዛዝን ተግባራዊ ማድረግ ይወደዳል።
ኢብኑ ሐጀር በፈትሑል ባሪይ ውስጥ እንዲህ ብለዋል: "በሰሑር የሚገኘው በረከት በበርካታ መንገዶች ይገኛል። ሰሑር መብላት ሱናን መከተል ነው፤ የመጽሐፉ ሰዎችን መቃረን ነው፤ ለአምልኮ ማጠናከሪያ ነው፤ ንቃትን የሚጨምር ነው፤ ረሃብ የሚያስከትለውን መነጫነጭ መከላከያ ነው፤ በዛን ወቅት ምፅዋት ለሚጠይቅ ሰው ወይም አብሮት ለሚበላ ሰው ለመመፅወት ምክንያት ነው፤ ዱዓ ተቀባይነት ያገኛል ተብሎ በሚታሰብበት በዚህ ወቅት ዱዓና ዚክር እንድናደርግ ምክንያት ነው፤ ከመተኛቱ በፊት ከመነየት ለተዘናጋ ሰው የጾሙን ኒያ እንዲነይት ምክንያት ነው።"
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ልብ ተደስቶ እንዲሰራውና የሸሪዓ ውበትን ለማሳወቅ ብያኔን ከጥበብ ጋር ማቆራኘታቸው የማስተማር ጥበባቸውን ያሳየናል።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «ሰሑር ሰውዬው በሚበላው ወይም በሚጠጣው ትንሽ ነገርም ይገኛል።»
ኢብኑ ሐጀር በፈትሑል ባሪይ ውስጥ እንዲህ ብለዋል: "በሰሑር የሚገኘው በረከት በበርካታ መንገዶች ይገኛል። ሰሑር መብላት ሱናን መከተል ነው፤ የመጽሐፉ ሰዎችን መቃረን ነው፤ ለአምልኮ ማጠናከሪያ ነው፤ ንቃትን የሚጨምር ነው፤ ረሃብ የሚያስከትለውን መነጫነጭ መከላከያ ነው፤ በዛን ወቅት ምፅዋት ለሚጠይቅ ሰው ወይም አብሮት ለሚበላ ሰው ለመመፅወት ምክንያት ነው፤ ዱዓ ተቀባይነት ያገኛል ተብሎ በሚታሰብበት በዚህ ወቅት ዱዓና ዚክር እንድናደርግ ምክንያት ነው፤ ከመተኛቱ በፊት ከመነየት ለተዘናጋ ሰው የጾሙን ኒያ እንዲነይት ምክንያት ነው።"
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ልብ ተደስቶ እንዲሰራውና የሸሪዓ ውበትን ለማሳወቅ ብያኔን ከጥበብ ጋር ማቆራኘታቸው የማስተማር ጥበባቸውን ያሳየናል።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «ሰሑር ሰውዬው በሚበላው ወይም በሚጠጣው ትንሽ ነገርም ይገኛል።»
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

