HadeethEnc · 1.23.0
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) አላህ ህይወታቸውን እስከወሰደባት ጊዜ ድረስ የረመዷን የመጨረሻዎቹ አስር ቀናቶችን ኢዕቲካፍ ያደርጉ ነበር። ከዚያም ከርሳቸው ህልፈት በኋላ ባለቤቶቻቸው ኢዕቲካፍ አድርገዋል።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
የአማኞች እናትና የነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ባለቤት ከሆነችው ከዓኢሻ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው: "ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) አላህ ህይወታቸውን እስከወሰደባት ጊዜ ድረስ የረመዷን የመጨረሻዎቹ አስር ቀናቶችን ኢዕቲካፍ ያደርጉ ነበር። ከዚያም ከርሳቸው ህልፈት በኋላ ባለቤቶቻቸው ኢዕቲካፍ አድርገዋል።"
02
Explanation
የአማኞች እናት ዓኢሻ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) ለይለተል ቀደርን በመፈለግ በመጨረሻዎቹ የረመዳን አስር ቀናቶች ኢዕቲካፍ በማድረግ እንደሚያሳልፉ ይህንንም አላህ ሩሓቸውን እስከወሰደበት ጊዜ ድረስ እንደቀጠሉበትና ከርሳቸው በኋላም ሚስቶቻቸው (ረዺየሏሁ ዐንሁነ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ኢዕቲካፍ ማድረጉን እንደቀጠሉበት ተናገረች።
03
Benefits
መስጂዶች ውስጥ ኢዕቲካፍ ማድረግ ለሴቶች እንኳን ሳይቀር የሸሪዓ ደንቦችን ካሟላች የተደነገገ ጉዳይ ነው። ይህ ግን ፈተና የማይገጥም ከሆነ ነው።
በረመዷን የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ላይ ኢዕቲካፍ ማድረግ ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) አዘውትረው ስለሰሩት አፅንኦት የተሰጠው አምልኮ ነው።
ከነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በኋላ ሚስቶቻቸው ኢዕቲካፍ ስላደረጉ ኢዕቲካፍ ያልተሻረ ቀጣይነት ያለው ሱንና መሆኑን እንረዳለን።
በረመዷን የመጨረሻዎቹ አስር ቀናት ላይ ኢዕቲካፍ ማድረግ ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) አዘውትረው ስለሰሩት አፅንኦት የተሰጠው አምልኮ ነው።
ከነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በኋላ ሚስቶቻቸው ኢዕቲካፍ ስላደረጉ ኢዕቲካፍ ያልተሻረ ቀጣይነት ያለው ሱንና መሆኑን እንረዳለን።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

