HadeethEnc · 1.23.0
ወንድምህ በዳይም ሆነ ወይም ተበዳይ እርዳው።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
አነስ ቢን ማሊክ -አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና- እንዳስተላለፉት እንዲህ አሉ: «የአላህ መልክተኛ - የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና - እንዲህ ብለዋል፦ "ወንድምህ በዳይም ሆነ ወይም ተበዳይ እርዳው።" አንድ ሰውዬም እንዲህ አለ: "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ተበዳይ የሆነ ጊዜ እረዳዋለሁ። እስኪ ንገሩኝ በዳይ በሆነ ጊዜ እንዴት ነው የምረዳው?" እርሳቸውም "ከመበደል ታቅበዋለህ ወይም ትከለክለዋለህ። ይህ እርሱን መርዳት ነው።" ብለው መለሱ።»
02
Explanation
ነቢዩ -የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና- ሙስሊም ወንድም በዳይም ሆነ ወይም ተበዳይ እንዲረዳ አዘዙ። አንድ ሰውዬም እንዲህ አለ: የአላህ መልክተኛ ሆይ! ተበዳይ በሆነ ጊዜ በደልን ከርሱ ላይ በማስወገድ እረዳዋለሁ። ንገሩኝ እስኪ በዳይ ከሆነ እንዴት ነው የምረዳው? እርሳቸውም እንዲህ በማለት መለሱ: ከበደል ትከለክለዋለህ፣ እጁን ትይዘዋለህ፣ ትገታዋለህ፣ ታቅበዋለህ። ይህ በሰይጣኑና በመጥፎ በምታዘው ነፍሱ ላይ እያገዝከው ነው።
03
Benefits
በሙስሊሞች መካከል የእምነታዊ ወንድማማችነት ሀቆች መካከል አንዱን ሀቅ ተገንዝበናል።
የበዳይን እጅ መያዝና ከበደል መከልከል እንደሚገባ እንረዳለን።
ተበዳዮች ሁነውም ይሁን በዳይ ሁነው እርስ በርስ ይረዳዱ የነበሩትን የድንቁርና አስተሳሰብ እስልምና ተፃሮ መምጣቱን እንረዳለን።
የበዳይን እጅ መያዝና ከበደል መከልከል እንደሚገባ እንረዳለን።
ተበዳዮች ሁነውም ይሁን በዳይ ሁነው እርስ በርስ ይረዳዱ የነበሩትን የድንቁርና አስተሳሰብ እስልምና ተፃሮ መምጣቱን እንረዳለን።
Attribution
[ቡኻሪ ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

