HadeethEnc · 1.23.0
'በእጅህ እንዲህ ብታደርግ በቂህ ነበር።' አሉና ከዚያም በሁለት እጃቸው መሬቱን አንድ ጊዜ መቱ። ከዚያም በግራ እጃቸው ቀኝ እጃቸውን አበሱ። የላይኛውን የመዳፋቸው ክፍልንና ፊታቸውን አበሱ።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከዓማር ቢን ያሲር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: "የአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለአንድ ጉዳይ ላኩኝና የዘር ፈሳሽ ወጣኝ። ውሃ አላገኘሁምና እንስሳ መሬት ላይ እንደምትንከባለለው ተንከባለልኩኝ። ከዚያም ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዘንድ መጣሁና ይህን ድርጊቴ አወሳሁላቸው። እርሳቸውም 'በእጅህ እንዲህ ብታደርግ በቂህ ነበር።' አሉና ከዚያም በሁለት እጃቸው መሬቱን አንድ ጊዜ መቱ። ከዚያም በግራ እጃቸው ቀኝ እጃቸውን አበሱ። የላይኛውን የመዳፋቸው ክፍልንና ፊታቸውን አበሱ።"
02
Explanation
ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዓማር ቢን ያሲርን (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - ለሆነ ጉዳይ ጉዞ ላኩት። በግንኙነት ወይም በተኛበት በስሜት የዘር ፈሳሽ በመውጣቱ ምክንያት ጀናባ አገኘው። የሚታጠብበት ውሃም አላገኘም። የሚያውቀው ዉዱእ ሲያጠፋ ለትንሹ ሐደሥ የሚደረገውን የተየሙም ብይን እንጂ ጀናባ ሲያጋጥም የሚደረገውን የተየሙም ብይን አያውቅም ነበር። ስለ አፈፃፀሙ ከተመራመረ በኋላ ዉዱእ ሲጠፋ የምድር ገፅ ላይ በሚገኝ አፈር ከፊል የዉዱእ አካላትን እንደሚታበሰው ለጀናባ የሚደረገው የተየሙም አፈፃፀም ደግሞ የግድ መላ ሰውነትን በአፈር ማዳረስ መሆን አለበት ብሎ አሰበ። ይህም በውሃ ቀይሶት ነው። ሰውነቱን ባጠቃላይ እንዲነካም አፈር ላይ ተንከባለለና ሰገደ። ወደ ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የመጣ ጊዜም ትክክል ነው የፈፀምኩት ወይስ አይደለም? የሚለውን ለማወቅ ያደረገውን አወሳላቸው። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከሁለቱም ሐደሦች ማለት እንደሽንት ካለው ዉዱእ የሚያጠፋው ትንሹ ሐደሥ እና እንደ ጀናባ ካለው ገላ የሚያስታጥበው ትልቁ ሐደሥ የአፀዳድ አፈፃፀምን ገለፁለት። እርሱም በሁለት እጆቹ አንድ ጊዜ አፈርን በመምታት ከዚያም በግራ እጁ ቀኝ እጁን ያብሳል፤ የመዳፎቹን የላይኛውን ክፍልና ፊቱን ያብሳል።
03
Benefits
ከተየሙም በፊት ውሃ መፈለግ ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
ጀናባ ላይ ሆኖ ውሃ ላላገኘ ሰው ተየሙም እንደተደነገገለት እንረዳለን።
ለትልቁ ሐደሥ የሚደረገው ተየሙም ለትንሹ ሐደሥ እንደሚደረገው ተየሙም እንደሆነ እንረዳለን።
ጀናባ ላይ ሆኖ ውሃ ላላገኘ ሰው ተየሙም እንደተደነገገለት እንረዳለን።
ለትልቁ ሐደሥ የሚደረገው ተየሙም ለትንሹ ሐደሥ እንደሚደረገው ተየሙም እንደሆነ እንረዳለን።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

