HadeethEnc · 1.23.0
አቡ በክር ሆይ! አላህ ሶስተኛቸው በሆኑ ሁለት ሰዎች ጉዳይ ምንድን ነው የምታስበው?" አሉ።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ በክር አስሲዲቅ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው እንዲህ አሉ: «እኛ ዋሻ ውስጥ ሆነን ሳለን የአጋርያን እግር ከጭንቅላታችን በላይ ሆኖ ተመለከትኩት። እኔም "የአላህ መልክተኛ ሆይ: ከአጋርያኖች መካከል አንዱ ወደ እግሮቹ ቢመለከት'ኮ ከእግሮቹ ስር ይመለከተን ነበር።" አልኳቸው። እርሳቸውም: "አቡ በክር ሆይ! አላህ ሶስተኛቸው በሆኑ ሁለት ሰዎች ጉዳይ ምንድን ነው የምታስበው?" አሉ።»
02
Explanation
የአማኞች መሪ አቡ በክር አስሲዲቅ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በስደት ወቅት ስለነበረው ሁኔታ ሲተርኩ እንዲህ አሉ: እኛ የሠውር ዋሻ ውስጥ ሆነን ሳለን ከጭንቅላታችን በላይ የአጋርያን እግር ሆኖ ተመለከትኩ። እኔም "የአላህ መልክተኛ ሆይ! ከአጋርያኖች መካከል አንዱ ወደ እግሮቹ ቢመለከት'ኮ ከእግሮቹ ስር ይመከተናል።" አልኳቸው። እርሳቸውም: "አቡ በክር ሆይ! አላህ በእርዳታው፣ በእገዛውና በጥበቃው ሶስተኛቸው በሆኑ ሁለት ሰዎች ጉዳይ ምንድን ነው የምታስበው?" አሉት።
03
Benefits
አቡበክር አስሲዲቅ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - የአላህን መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ከመካ ወደ መዲና በሚሰደዱበት ወቅት ቤተሰብና ገንዘባቸውን ትተው መጎዳኘታቸው የነበራቸውን ማዕረግ ያሳየናል።
አቡ በክር አስሲዲቅ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በወቅቱ የነበራቸውን ስጋት፣ ለአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የነበራቸውን ጥልቅ ውዴታና ጠላቶች እርሳቸውን እንዳያጠቁ የነበራቸውን ስጋት እንመለከታለን።
በአላህ ላይ መተማመንና ጥንቃቄን በመያዝ ጥረት ካደረጉ በኋላ በርሱ ጥበቃና እንክብካቤ መረጋጋት ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
አላህ ለነቢያቶቹና ለወዳጆቹ ትኩረት መስጠቱንና ለነርሱም በእርዳታው እንደሚንከባከባቸው እንረዳለን። አላህ እንዲህ ብሏል: {እኛ መልክተኞቻችንን፣ እነዚያንም ያመኑትን በቅርቢቱ ህይወት ምስክሮችም በሚቆሙበት ቀን በእርግጥ እንረዳለን።}
ይህ ሐዲሥ በአላህ ላይ የተመካ ሰው አላህ እንደሚበቃው፣ እንደሚረዳው፣ እንደሚያግዘውና እንደሚጠብቀው ያስገነዝበናል።
ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በጌታቸው ላይ ያላቸው የተሟላ መመካትን እንረዳለን። እርሳቸው በአላህ ላይ የሚመኩና ጉዳያቸውን ሁሉ ወደርሱ የሚያስጠጉ ነበሩ።
የነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ጀግንነትና ቀልብና ነፍስን ያረጋጉ እንደነበር እንረዳለን።
ጠላትን በመፍራት ሃያማኖትን አስጠብቆ መሸሽና ሰበብንም ማድረስ እንደሚገባ እንረዳለን።
አቡ በክር አስሲዲቅ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - በወቅቱ የነበራቸውን ስጋት፣ ለአላህ መልክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የነበራቸውን ጥልቅ ውዴታና ጠላቶች እርሳቸውን እንዳያጠቁ የነበራቸውን ስጋት እንመለከታለን።
በአላህ ላይ መተማመንና ጥንቃቄን በመያዝ ጥረት ካደረጉ በኋላ በርሱ ጥበቃና እንክብካቤ መረጋጋት ግዴታ መሆኑን እንረዳለን።
አላህ ለነቢያቶቹና ለወዳጆቹ ትኩረት መስጠቱንና ለነርሱም በእርዳታው እንደሚንከባከባቸው እንረዳለን። አላህ እንዲህ ብሏል: {እኛ መልክተኞቻችንን፣ እነዚያንም ያመኑትን በቅርቢቱ ህይወት ምስክሮችም በሚቆሙበት ቀን በእርግጥ እንረዳለን።}
ይህ ሐዲሥ በአላህ ላይ የተመካ ሰው አላህ እንደሚበቃው፣ እንደሚረዳው፣ እንደሚያግዘውና እንደሚጠብቀው ያስገነዝበናል።
ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በጌታቸው ላይ ያላቸው የተሟላ መመካትን እንረዳለን። እርሳቸው በአላህ ላይ የሚመኩና ጉዳያቸውን ሁሉ ወደርሱ የሚያስጠጉ ነበሩ።
የነቢዩን (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ጀግንነትና ቀልብና ነፍስን ያረጋጉ እንደነበር እንረዳለን።
ጠላትን በመፍራት ሃያማኖትን አስጠብቆ መሸሽና ሰበብንም ማድረስ እንደሚገባ እንረዳለን።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

