HadeethEnc · 1.23.0
ጀናዛን ከመሸኘት ተከልክለናል። አፅንዖት ሰጥተው ግን አልከለከሉንም።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከኡሙ ዐጢየህ - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ አለች: "ጀናዛን ከመሸኘት ተከልክለናል። አፅንዖት ሰጥተው ግን አልከለከሉንም።"
02
Explanation
ኡሙ ዐጢየህ አልአንሷሪየህ (አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና) ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሴቶች ጀናዛን ለመሸኘት አብረው ከመሄድ እንደተከለከሉ ተናገረች። ይህም ለነርሱም ይሁን በነርሱ ምክንያት ፈተና ይከሰታል ተብሎ ስለተፈራና ትእግስታቸው ያነሰ ስለሆነ ነው። ቀጥላም (አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና) ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ሌሎች ክልከላዎች ላይ እንደሚያከብዱት ይህንን ግን ክብደት ሰጥተው አልከለከሉም አለች።
03
Benefits
ሴቶች ጀናዛን ከመሸኘት መከልከላቸውን እንረዳለን። ይህም ጀናዛው ወደሚሰናዳበትም ወደሚሰገድብትም ይሁን ወደ መቃብር ስፍራ ሲሄድ ያለውን መከተል ሁሉ የሚያካትት ክልከላ ነው።
የክልከላው ምክንያትም ሴቶች እንደዚህ አይነት የሚያሳዝን ሁኔታዎችና ልብ የሚነካ አጋጣሚዎችን መቋቋም ስለማይችሉ በዚህም ሰበብ ምንአልባት ግዴታቸው የሆነውን ትእግስት የሚፃረር ማማረርና ትእግስት ማጣት ሊታይባቸው ስለሚችል ነው።
ክልከላ በመሰረቱ እርምነትን (ሐራምነትን) ነው የሚጠቁመው። ነገር ግን ኡሙ ዐጢየህ (አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና) በጊዜው ከነበረው የአነጋገር ሁኔታ ጀናዛን ከመሸኘት መከልከላቸው አፅንዖት የተሰጠው ቁርጥ ክልከላ እንዳልሆነ ተረዳች። ነገር ግን ጀናዛን የመሸኘት ክልከላው ጠንከር ያለ መሆኑን የሚጠቁሙ ይህ ሐዲሥ ከሚጠቁመው የበለጠ በርካታ ሐዲሦች መጥተዋል።
የክልከላው ምክንያትም ሴቶች እንደዚህ አይነት የሚያሳዝን ሁኔታዎችና ልብ የሚነካ አጋጣሚዎችን መቋቋም ስለማይችሉ በዚህም ሰበብ ምንአልባት ግዴታቸው የሆነውን ትእግስት የሚፃረር ማማረርና ትእግስት ማጣት ሊታይባቸው ስለሚችል ነው።
ክልከላ በመሰረቱ እርምነትን (ሐራምነትን) ነው የሚጠቁመው። ነገር ግን ኡሙ ዐጢየህ (አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና) በጊዜው ከነበረው የአነጋገር ሁኔታ ጀናዛን ከመሸኘት መከልከላቸው አፅንዖት የተሰጠው ቁርጥ ክልከላ እንዳልሆነ ተረዳች። ነገር ግን ጀናዛን የመሸኘት ክልከላው ጠንከር ያለ መሆኑን የሚጠቁሙ ይህ ሐዲሥ ከሚጠቁመው የበለጠ በርካታ ሐዲሦች መጥተዋል።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

