አንድ ሙስሊም ሰው ለወንድሙ ከሩቅ (በሌለበት) የሚያደርግለት ዱዓ ተቀባይነት አለው።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከኡሙ ደርዳ እና ከአቡ ደርዳእ - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) እንዲህ ይሉ ነበር: «አንድ ሙስሊም ሰው ለወንድሙ ከሩቅ (በሌለበት) የሚያደርግለት ዱዓ ተቀባይነት አለው። ከጭንቅላቱ በላይ የተወከለ መልአክ አለ። ለወንድሙ መልካም ነገርን ዱዓ ባደረገለት ቁጥር ለዚህ ጉዳይ የተወከለው መልአክም "አሚን ላንተም ተመሳሳዩ አለህ።" ይለዋል።»
Explanation
Benefits
ከሩቅ ዱዓ ማድረግ እውነተኛ ኢማንና ወንድማማችነት እንዳለ ፍንትው አድርጎ ያሳያል።
ዱዓ ማድረግን ከሩቅ በሚለው መገደቡ ጥግ ለደረሰ ኢኽላስና ተመስጦ ምቹ ስለሆነ ነው።
ዱዓ ተቀባይነት ከሚያገኝባቸው ምክንያቶች መካከል አንዱ አንድ ሙስሊም ለወንድሙ ከሩቅ ዱዓ ማድረጉ ነው።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "ከሩቅ በሌለበት ለሙስሊም ወንድም ዱዓ ማድረግ ያለውን ደረጃ እንረዳለን። ዱዓውን ያደረገው ለበርካታ የሙስሊም ጀመዓዎች ቢሆንም ይህን ደረጃ ያገኛል። ለሙስሊሞች ባጠቃላይም ቢያደርግም የሐዲሡ ግልፅ መልዕክት እንደሚያሳየው አሁንም ይህን ደረጃ ያገኛል። አንዳንድ ቀደምቶች ለራሳቸው ዱዓ ማድረግ በሚፈልጉበት ወቅት ዱዓቸው ተቀባይነት እንዲያገኝና የዱዓውን ተመሳሳዩን ስለሚያስገኝላቸው ያቺን ለራሳቸው የፈለጓትን ነገር ለሙስሊም ወንድማቸው ዱዓ ያደርጉ ነበር።"
አንዱ የመልአኮች ተግባር ተገልጿል። ከመልአኮች መካከል አላህ ለዚህ ሥራ የወከለው አለ።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

