‹ከፈለግሽ ታግሰሽ ላንቺ ጀነት አለሽ። ከፈለግሽ ደሞ ጤናን እንዲለግስሽ አላህን እለምንልሻለሁኝ።›
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከኢብኑ ዐባስ -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: ኢብኑ ዓባስ ለዐጧእ ቢን አቢ ረባሕ እንዲህ አሉ:«ከጀነት ሰዎች መካከል የሆነች ሴት አላሳይህምን?" እኔም "እንዴታ!" አልኩኝ። እርሳቸውም እንዲህ አሉኝ: "ይህቺ ጥቁር ሴት ናት። ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በርሳቸው ላይ ይስፈንና) ዘንድ መጣችና እንዲህ አለች: ‹እኔ የሚጥል በሽታ አለብኝና እገላለጣለሁ። እንዲፈውሰኝ አላህን ለምኑልኝ።› እርሳቸውም: ‹ከፈለግሽ ታግሰሽ ላንቺ ጀነት አለሽ። ከፈለግሽ ደሞ ጤናን እንዲለግስሽ አላህን እለምንልሻለሁኝ።› አሏት። እርሷም ‹እታገሳለሁ።› ብላ እንዲህም አለች: ‹እኔ እገላለጣለሁኝ። እንዳልገላለጥ አላህን ለምኑልኝ።› እርሳቸውም ዱዓ አደረጉላት።"»
Explanation
Benefits
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ የሚጥል በሽታ የተሟላን ምንዳ እንደሚያስመነዳ ይጠቁማል።"
ሴት ሶሓቦች (አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና) የነበራቸውን ሀፍረትና ጥብቅነት እንዲሁም ለመሸፈን የነበራቸውን ጥረት እንረዳለን። ይህቺ ሴት አብዝታ ትፈራ የነበረው ጉዳይ ከሰውነቷ አንዳች አካል እንዳይገለጥባት ነበር።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ነፍሱ አቅም እንዳላት የተረዳና በጠንካራው ትእዛዝ ለመዘውተር ያልደከመ ሰው የተግራራውን ትእዛዝ ከመተግበር ይልቅ ጠንካራውን ትእዛዝ መተግበሩ ይበልጥለታል።"
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ በሽታዎችን ሁሉ በዱዓ፣ ወደ አላህ በመጠጋት ማከም በመድሓኒቶች ከመፈወስ የበለጠ ፈዋሽና ጠቃሚ እንደሆነ፣ የዱዓ ተፅእኖና የሚፈጥረው አካላዊ መነቃቃትም መድሃኒቶች ከሚፈጥሩት ተፅእኖ እጅግ የላቀ እንደሆነ እንረዳለን። ነገር ግን ይህ ስኬታማ የሚሆነው ሁለት ነገሮች ሲሟሉ ነው: የመጀመሪያው የሚፈለገው ከታማሚው ሲሆን እርሱም: በትክክል እድናለሁኝ የሚል ሃሳብ መሰነቅ ነው። ሁለተኛው: ከሚያክመው ሰው የሚፈለግ ሲሆን: ወደ አላህ የዞረበት ጥንካሬና ቀልቡ አላህን በመፍራትና በአላህ በመመካት የበረታ መሆኑ ነው።" አላህ የበለጠ አዋቂ ነው።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "ይህ ሐዲሥ ህክምናን መተውም እንደሚፈቀድ ይጠቁማል።"
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

