HadeethEnc · 1.23.0
የነቢዩን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንጥላቸውን እስክመለከት ድረስ በጭራሽ ሙሉ አፋቸውን ከፍተው ሲስቁ ተመልክቻቸው አላውቅም። ሲስቁ ፈገግ ብቻ ነበር የሚሉት
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአማኞች እናት ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው እንዲህ አለች: "የነቢዩን (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና እንጥላቸውን እስክመለከት ድረስ በጭራሽ ሙሉ አፋቸውን ከፍተው ሲስቁ ተመልክቻቸው አላውቅም። ሲስቁ ፈገግ ብቻ ነበር የሚሉት"
02
Explanation
ዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ሳቃቸው እንጥላቸው እስኪታይ ድረስ ከመጠን ያለፈ እንዳልነበር፤ ከሳቁም ፈገግ ብቻ ይሉ እንደነበር ተናገረች። እንጥል ማለት ከጉሮሮ በላይ የተንጠለጠለ ስጋ ነው።
03
Benefits
የአላህ መልክተኛ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና አንዳች ነገር ከተመቻቸው ወይም የተደሰቱበት ጊዜ የሚስቁት ሳቅ ፈገግታ ነበር።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «"በሳቅ ጉዳይ በሙሉ አፋቸው ሲስቁ አላየኃቸውም" ማለት ለመሳቅ ሙሉ ለሙሉ ዝግጁ ሆነው የተሟላ ሳቅ ሲስቁ ማለት ነው።»
ሳቅ ማብዛትና በመንተክተክ ድምፅን ከፍ ማድረግ የደጋጎች ባህሪ አይደለም።
ሳቅ ማብዛት ሰውዬው በወንድሞቹ መካከል ያለውን ግርማና ክብር ይቀንስበታል።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: «"በሳቅ ጉዳይ በሙሉ አፋቸው ሲስቁ አላየኃቸውም" ማለት ለመሳቅ ሙሉ ለሙሉ ዝግጁ ሆነው የተሟላ ሳቅ ሲስቁ ማለት ነው።»
ሳቅ ማብዛትና በመንተክተክ ድምፅን ከፍ ማድረግ የደጋጎች ባህሪ አይደለም።
ሳቅ ማብዛት ሰውዬው በወንድሞቹ መካከል ያለውን ግርማና ክብር ይቀንስበታል።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

