HadeethEnc · 1.23.0
(አላህን በማመፁ ምክንያት) አላህ ያስቀመጠው የቅጣት ወሰን ካልሆነ በቀር (ስርአት ለማስያዝ) ተብሎ አንድም ሰው ከአስር አለንጋ በላይ እንዳይገረፍ።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ከአቡ ቡርዳህ አልአንሷሪይ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና - እንደተላለፈው: እርሱ የአላህን መልዕክተኛ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) እንዲህ ሲሉ ሰማ፦ "(አላህን በማመፁ ምክንያት) አላህ ያስቀመጠው የቅጣት ወሰን ካልሆነ በቀር (ስርአት ለማስያዝ) ተብሎ አንድም ሰው ከአስር አለንጋ በላይ እንዳይገረፍ።"
02
Explanation
ነቢዩ (የአላህ ሰላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈን) በወንጀል ላይ ካልሆነ በቀር አንድም ሰው ከአስር አለንጋ በላይ መገረፉን ከለከሉ። ሐዲሡ ውስጥ የተፈለገው በቁጥር ተገድበው ከአላህና ከመልክተኛው የመጡ ግርፋቶች ወይም ምቶች ወይም ልዩ ቅጣቶችን አይደለም። ይልቁንም በሐዲሡ የተፈለገው ስርአት ለማስያዝ ሲባል ሚስትንና ልጅን መግረፍ ቢያስፈልግ ከአስር አለንጋ አይጨምር ማለት ነው።
03
Benefits
አላህ ያዘዘባቸው ወይም የከለከላቸው የአላህ ድንበሮች እነርሱን ከመተላለፍ የሚያስጠነቅቁ የሆኑ ቅጣቶች አሏቸው። እነዚህ ቅጣቶችም ወይ ከራሱ ከአላህ የተወሰኑ ናቸው ወይም ደግሞ ዳኛው የተሻለ ነው ብሎ እንደሚያየው ይወሰናል።
ስርአት ማስያዣ ቅጣቶች ለማስፈራሪያና ትክክለኛውን አቅጣጫ ለማሳየት ያህል ቀለል ያሉ መሆን አለባቸው። የግድ መምታት ካስፈለገም ከአስር አለንጋ መጨመር የለበትም። በላጩም ያለዱላ ትክክለኛውን በመጠቆም፣ በማስተማር፣ በመምራትና በማበረታታት ስርአት ማስያዝ ነው። ይህም ትምህርቱን እንዲቀበሉና መማማሩም የለሰለሰ እንዲሆን የተሻለው መንገድ ነው። በነዚህ ሁኔታዎች የምናደርጋቸው ነገሮች ብዙ ጊዜ ይለያያሉ። ነገር ግን የተሻለውን አይቶ ማድረግ ተገቢ ነው።
ስርአት ማስያዣ ቅጣቶች ለማስፈራሪያና ትክክለኛውን አቅጣጫ ለማሳየት ያህል ቀለል ያሉ መሆን አለባቸው። የግድ መምታት ካስፈለገም ከአስር አለንጋ መጨመር የለበትም። በላጩም ያለዱላ ትክክለኛውን በመጠቆም፣ በማስተማር፣ በመምራትና በማበረታታት ስርአት ማስያዝ ነው። ይህም ትምህርቱን እንዲቀበሉና መማማሩም የለሰለሰ እንዲሆን የተሻለው መንገድ ነው። በነዚህ ሁኔታዎች የምናደርጋቸው ነገሮች ብዙ ጊዜ ይለያያሉ። ነገር ግን የተሻለውን አይቶ ማድረግ ተገቢ ነው።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

