ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለኡዱሒያ ሁለት ቡራቡሬና ቀንዳም የሆኑ ሙክቶችን በእጃቸው አረዱ። "ቢስሚላህ አላሁ አክበር" አሉና እግራቸውን አንገቱ ላይ አድርገው አረዱት።
Choose an available translation of this Hadeeth
Hadeeth text
ከአነስ (ረዲየሏሁ ዐንሁ) - አላህ መልካም ሥራቸውን ይውደድላቸውና እንደተላለፈው እንዲህ ብለዋል: «ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ለኡዱሒያ ሁለት ቡራቡሬና ቀንዳም የሆኑ ሙክቶችን በእጃቸው አረዱ። "ቢስሚላህ አላሁ አክበር" አሉና እግራቸውን አንገቱ ላይ አድርገው አረዱት።»
Explanation
Benefits
ኡዱሒያው ነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) ያረዱት አይነት መሆኑ በላጭ ነው። ይህም ሲታይ ስለሚያምርና ሞራውና ስጋውም ጣፋጭ ስለሚሆን ነው።
ነወዊይ እንዲህ ብለዋል: «በዚህ ሐዲሥ መሰረት አንድ ሰው ኡዱሒያውን በራሱ ማረድ እንደሚገባውና በቂ ምክንያት ሳይኖረው ለማረድ ሰው መወከል እንደሌለበት እንረዳለን። በቂ ምክንያት ካለው ግን ሲታረድ መገኘቱ ይወደድለታል። በርሱ ፋንታ እንዲያርድለት ሙስሊም ሰው ከተካ ያለምንም ልዩነት ይፈቀዳል።
ኢብኑ ሐጀር እንዲህ ብለዋል: "በዚህ ሐዲሥ ውስጥ በማረድ ወቅት ቢስሚላህ ከማለት ጋር አላሁ አክበር ማለት እንደሚወደድ፤ እግርን ደሞ በሚታረደው ቀኝ የአንገቱ ክፍል ላይ ማኖር እንደሚወደድ እንረዳለን። የሚታረደውን የምናስተኛው በግራ ጎኑ በመሆኑ ዑለሞች ተስማምተዋል። ለአራጁ ቢላን በቀኝ እጅ መያዝ፣ በግራ እጁ ደግሞ ጭንቅላቱን መያዝ እንዲቀለው እግሩን በሚታረደው እንስሳ ቀኝ አንገት ላይ ያደርጋል።"
ለኡዱሒያ ቀንዳሙን ማረድ እንደሚወደድ እንረዳለን። ቀንድ ከሌለውም ግን ይፈቀዳል።
Attribution
Categories
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

