HadeethEnc · 1.23.0
ከስለት ከለከሉ። እንዲህም አሉ "እርሱ መልካምን ይዞ አይመጣም። በስለት የሚገኘው ትርፍ ስስታም ተገዶ ማውጣቱ ብቻ ነው።
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
ኢብኑ ዑመር (ረዲየሏሁ ዐንሁማ) -አላህ መልካም ስራቸውን ይውደድላቸውና- እንዳስተላለፉት: ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) ‐ የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ‐ ከስለት ከለከሉ። እንዲህም አሉ "እርሱ መልካምን ይዞ አይመጣም። በስለት የሚገኘው ትርፍ ስስታም ተገዶ ማውጣቱ ብቻ ነው።"
02
Explanation
ነቢዩ (ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም) የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና ከስለት ከለከሉ። ይህም አንድ ሰው አላህ ግዴታ ያላደረገበትን ነገር በራሱ ላይ ግዴታ ማድረጉ ማለት ነው። እንዲህም አሉ: ስለት አንድን ነገር አያመጣምም አያዘገይምም። ከስለት የሚገኘው ግዴታ የሆነበትን ነገር ካልሆነ በቀር የማይፈፅምን የሆነ ስስታም ሰው ተገዶ እንዲያወጣ ማስድረጉ ነው። ስለት ያልተወሰነልህን ነገር አያመጣም።
03
Benefits
ስለት መሳል አልተደነገገም፤ ነገር ግን ከወንጀል ውጪ ከተሳለ ስለቱን መሙላት ግዴታው ነው።
የክልከላው ምክንያት (ስለት መልካምን ይዞ አይመጣም) ማለትም ከአላህ ውሳኔ አንዳችንም አይመልስምና፤ የተሳለው ሰውም ፍላጎቱ የተሟላው በስለቱ ምክንያት መሆኑን እንዳያስብ ነው። አላህ ከዚህ የተብቃቃ ነውና።
ቁርጡቢ እንዲህ ብለዋል: «ይህ ክልከላ ለምሳሌ እንዲህ ማለቱን ነው: "አላህ የታመመብኝን ከፈወሰልኝ እኔ ላይ እንዲህ ያህል ምፅዋት አለብኝ።" ይህ የተጠላበትም ምክንያት የተጠቀሰውን አምልኮ መፈፀም ከተጠቀሰው አላማ መሳካት ጋር ያቆራኘ በመሆኑ ከርሱ የሚመነጨው ተግባር ወደ አላህ በመቃረብ ኒያ ሳይሆን ይልቁኑም የሄደበት መንገድ የመለዋወጥ ስልት መሆኑ ግልፅ ነው። ይህንንም የበለጠ ግልፅ የሚያደርግልን ታማሚው ባይፈወስለት ኖሮ በመፈወሱ ምክንያት ያወጣው የነበረውን ምፅዋት አለማውጣቱ ነው። ይህ ደግሞ የስስታሞች መገለጫ ነው። አብዛኛውን ጊዜ ስስታም ሰው ከሚያወጣው ወጪ በላይ ተለዋጭ ጥቅም በወቅቱ እስካላስገኘለት ድረስ ከገንዘቡ አንዳችንም አያወጣምና።
የክልከላው ምክንያት (ስለት መልካምን ይዞ አይመጣም) ማለትም ከአላህ ውሳኔ አንዳችንም አይመልስምና፤ የተሳለው ሰውም ፍላጎቱ የተሟላው በስለቱ ምክንያት መሆኑን እንዳያስብ ነው። አላህ ከዚህ የተብቃቃ ነውና።
ቁርጡቢ እንዲህ ብለዋል: «ይህ ክልከላ ለምሳሌ እንዲህ ማለቱን ነው: "አላህ የታመመብኝን ከፈወሰልኝ እኔ ላይ እንዲህ ያህል ምፅዋት አለብኝ።" ይህ የተጠላበትም ምክንያት የተጠቀሰውን አምልኮ መፈፀም ከተጠቀሰው አላማ መሳካት ጋር ያቆራኘ በመሆኑ ከርሱ የሚመነጨው ተግባር ወደ አላህ በመቃረብ ኒያ ሳይሆን ይልቁኑም የሄደበት መንገድ የመለዋወጥ ስልት መሆኑ ግልፅ ነው። ይህንንም የበለጠ ግልፅ የሚያደርግልን ታማሚው ባይፈወስለት ኖሮ በመፈወሱ ምክንያት ያወጣው የነበረውን ምፅዋት አለማውጣቱ ነው። ይህ ደግሞ የስስታሞች መገለጫ ነው። አብዛኛውን ጊዜ ስስታም ሰው ከሚያወጣው ወጪ በላይ ተለዋጭ ጥቅም በወቅቱ እስካላስገኘለት ድረስ ከገንዘቡ አንዳችንም አያወጣምና።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

