HadeethEnc · 1.23.0
እነዚህ ከመካከላቸው መልካም (ጻድቅ) ባርያ ወይም መልካም ሰው ሲሞት በመቃብሩ ላይ መስገጃን የሚገነቡና
Available translations
Choose an available translation of this Hadeeth
01
Hadeeth text
የአማኞች እናት ከሆነችው ከዓኢሻ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - እንደተላለፈው፦ ኡሙ ሰላማ ለአላህ መልዕክተኛ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) በሀበሻ ምድር ማሪያህ በምትባል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስላየቻቸው ምስሎች ነገረቻቸው። የአላህ መልዕክተኛም ሶለላሁ ዐለይሂ ወሰለም እንዲህ አሉ፡- "እነዚህ ከመካከላቸው መልካም (ጻድቅ) ባርያ ወይም መልካም ሰው ሲሞት በመቃብሩ ላይ መስገጃን የሚገነቡና በውስጡም (ምስሉን) ስእላ ስእል የሚቀርፁ ናቸው። እነዚህ ህዝቦች አላህ ዘንድ እጅግ ክፉ (መጥፎ) ፍጡራን ናቸው።"
02
Explanation
የአማኞች እናት ኡሙ ሰለማ (ረዲየሏሁ ዐንሃ) - አላህ መልካም ሥራዋን ይውደድላትና - በሐበሻ ምድር ማሪያህ በምትባል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስእሎች፣ ጌጦችና ቅርፆች ማየቷን በመደነቅ ለነቢዩ (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) አወሳች። ነቢዩም (የአላህ ሶላትና ሰላም በእርሳቸው ላይ ይስፈንና) የነዚህን ስእሎች መደረግ ምክንያት ገለፁ። "እነዚህ አሁን አንቺ የምታወሺያቸው በመካከላቸው ደግ ሰው የሞተ ጊዜ በቀብሩ ላይ መስጂድ ይገነቡና በውስጡ ይሰግዱበታልም እነዚህንም ስእሎች ይስላሉ።" አሉ። ይህንን የሚፈጽም ሰው አላህ ዘንድ ክፉ ፍጡር እንደሆነ ገለፁ። ምክንያቱም ይህ ድርጊቱ በአላህ ወደ ማጋራት ስለሚያዳርስ ነው።
03
Benefits
ወደ ሺርክ የሚያደርስን መንገድ ለመዝጋት ሲባል በመቃብሮች ላይ መስጊዶች መገንባት ወይም እርሷ ዘንድ መስገድ ወይም መስጊድ ውስጥ ሟቾችን መቅበር ክልክል ነው።
መቃብሮች ላይ መስጂዶችን መገንባትና ስእሎችን መስጅድ ውስጥ መስቀል የአይሁድና ክርስቲያኖች ስራ መሆኑንና ይህንን የፈፀመም ከነርሱ ጋር መመሳሰሉን እንረዳለን።
ነፍስ ያላቸውን ነገሮች ስእል መያዝ ክልክል መሆኑ።
ቀብር ላይ መስጂድ የገነባ፣ መስጂድ ውስጥም (ነፍስ ያላቸው) ስእሎችን የሳለ ሰው ከክፉዎቹ የአላህ ፍጡሮች መካከል የሚመደብ ነው።
ሸሪዓ ወደ ሺርክ የሚያደርሱ መንገዶችን ባጠቃላይ በመዝጋቱ ሸሪዓ የተውሒድን ዳር ድንበር ሙሉ ለሙሉ መጠበቁን እንረዳለን።
በደጋጎች ላይ ወሰን ማለፍ ሺርክ ላይ ለመውደቅ ምክንያት ስለሆነ ክልክል ነው።
መቃብሮች ላይ መስጂዶችን መገንባትና ስእሎችን መስጅድ ውስጥ መስቀል የአይሁድና ክርስቲያኖች ስራ መሆኑንና ይህንን የፈፀመም ከነርሱ ጋር መመሳሰሉን እንረዳለን።
ነፍስ ያላቸውን ነገሮች ስእል መያዝ ክልክል መሆኑ።
ቀብር ላይ መስጂድ የገነባ፣ መስጂድ ውስጥም (ነፍስ ያላቸው) ስእሎችን የሳለ ሰው ከክፉዎቹ የአላህ ፍጡሮች መካከል የሚመደብ ነው።
ሸሪዓ ወደ ሺርክ የሚያደርሱ መንገዶችን ባጠቃላይ በመዝጋቱ ሸሪዓ የተውሒድን ዳር ድንበር ሙሉ ለሙሉ መጠበቁን እንረዳለን።
በደጋጎች ላይ ወሰን ማለፍ ሺርክ ላይ ለመውደቅ ምክንያት ስለሆነ ክልክል ነው።
Attribution
[ቡኻሪና ሙስሊም ዘግበውታል።]
Categories
Share
Share hadeeth
Sharing options · 0 Total shares

