الفجر
Al-Fajr
The Dawn
1 - Al-Fajr (The Dawn) - 001
وَٱلۡفَجۡرِ
በጎህ እምላለሁ፡፡
2 - Al-Fajr (The Dawn) - 002
وَلَيَالٍ عَشۡرٖ
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡
3 - Al-Fajr (The Dawn) - 003
وَٱلشَّفۡعِ وَٱلۡوَتۡرِ
በጥንዱም በነጠላውም፡፡
4 - Al-Fajr (The Dawn) - 004
وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَسۡرِ
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡
5 - Al-Fajr (The Dawn) - 005
هَلۡ فِي ذَٰلِكَ قَسَمٞ لِّذِي حِجۡرٍ
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?
6 - Al-Fajr (The Dawn) - 006
أَلَمۡ تَرَ كَيۡفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِعَادٍ
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?
7 - Al-Fajr (The Dawn) - 007
إِرَمَ ذَاتِ ٱلۡعِمَادِ
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡
8 - Al-Fajr (The Dawn) - 008
ٱلَّتِي لَمۡ يُخۡلَقۡ مِثۡلُهَا فِي ٱلۡبِلَٰدِ
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡
9 - Al-Fajr (The Dawn) - 009
وَثَمُودَ ٱلَّذِينَ جَابُواْ ٱلصَّخۡرَ بِٱلۡوَادِ
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡
10 - Al-Fajr (The Dawn) - 010
وَفِرۡعَوۡنَ ذِي ٱلۡأَوۡتَادِ
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡
11 - Al-Fajr (The Dawn) - 011
ٱلَّذِينَ طَغَوۡاْ فِي ٱلۡبِلَٰدِ
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡
12 - Al-Fajr (The Dawn) - 012
فَأَكۡثَرُواْ فِيهَا ٱلۡفَسَادَ
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)
13 - Al-Fajr (The Dawn) - 013
فَصَبَّ عَلَيۡهِمۡ رَبُّكَ سَوۡطَ عَذَابٍ
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡
14 - Al-Fajr (The Dawn) - 014
إِنَّ رَبَّكَ لَبِٱلۡمِرۡصَادِ
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡
15 - Al-Fajr (The Dawn) - 015
فَأَمَّا ٱلۡإِنسَٰنُ إِذَا مَا ٱبۡتَلَىٰهُ رَبُّهُۥ فَأَكۡرَمَهُۥ وَنَعَّمَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّيٓ أَكۡرَمَنِ
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡
16 - Al-Fajr (The Dawn) - 016
وَأَمَّآ إِذَا مَا ٱبۡتَلَىٰهُ فَقَدَرَ عَلَيۡهِ رِزۡقَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّيٓ أَهَٰنَنِ
በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡
17 - Al-Fajr (The Dawn) - 017
كَلَّاۖ بَل لَّا تُكۡرِمُونَ ٱلۡيَتِيمَ
ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡
18 - Al-Fajr (The Dawn) - 018
وَلَا تَحَـٰٓضُّونَ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ
ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡
19 - Al-Fajr (The Dawn) - 019
وَتَأۡكُلُونَ ٱلتُّرَاثَ أَكۡلٗا لَّمّٗا
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡
20 - Al-Fajr (The Dawn) - 020
وَتُحِبُّونَ ٱلۡمَالَ حُبّٗا جَمّٗا
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡
21 - Al-Fajr (The Dawn) - 021
كَلَّآۖ إِذَا دُكَّتِ ٱلۡأَرۡضُ دَكّٗا دَكّٗا
ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤
22 - Al-Fajr (The Dawn) - 022
وَجَآءَ رَبُّكَ وَٱلۡمَلَكُ صَفّٗا صَفّٗا
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ለሱ ክብር በምስማማ መልኩ) በመጣ ጊዜ፤
23 - Al-Fajr (The Dawn) - 023
وَجِاْيٓءَ يَوۡمَئِذِۭ بِجَهَنَّمَۚ يَوۡمَئِذٖ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ وَأَنَّىٰ لَهُ ٱلذِّكۡرَىٰ
ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?
24 - Al-Fajr (The Dawn) - 024
يَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي قَدَّمۡتُ لِحَيَاتِي
«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡
25 - Al-Fajr (The Dawn) - 025
فَيَوۡمَئِذٖ لَّا يُعَذِّبُ عَذَابَهُۥٓ أَحَدٞ
በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡
26 - Al-Fajr (The Dawn) - 026
وَلَا يُوثِقُ وَثَاقَهُۥٓ أَحَدٞ
የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡
27 - Al-Fajr (The Dawn) - 027
يَـٰٓأَيَّتُهَا ٱلنَّفۡسُ ٱلۡمُطۡمَئِنَّةُ
(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!
28 - Al-Fajr (The Dawn) - 028
ٱرۡجِعِيٓ إِلَىٰ رَبِّكِ رَاضِيَةٗ مَّرۡضِيَّةٗ
«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡
29 - Al-Fajr (The Dawn) - 029
فَٱدۡخُلِي فِي عِبَٰدِي
«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡
30 - Al-Fajr (The Dawn) - 030