الفجر

 

Al-Fajr

 

The Dawn

1 - Al-Fajr (The Dawn) - 001

وَٱلۡفَجۡرِ
በጎህ እምላለሁ፡፡

2 - Al-Fajr (The Dawn) - 002

وَلَيَالٍ عَشۡرٖ
በዐሥር ሌሊቶችም፡፡

3 - Al-Fajr (The Dawn) - 003

وَٱلشَّفۡعِ وَٱلۡوَتۡرِ
በጥንዱም በነጠላውም፡፡

4 - Al-Fajr (The Dawn) - 004

وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَسۡرِ
በሌሊቱም በሚኼድ ጊዜ፡፡

5 - Al-Fajr (The Dawn) - 005

هَلۡ فِي ذَٰلِكَ قَسَمٞ لِّذِي حِجۡرٍ
በዚህ (መሓላ) ለባለ አእምሮ ታላቅ መሓላ አለበትን?

6 - Al-Fajr (The Dawn) - 006

أَلَمۡ تَرَ كَيۡفَ فَعَلَ رَبُّكَ بِعَادٍ
ጌታህ በዓድ እንዴት እንደ ሠራ አታውቅምን?

7 - Al-Fajr (The Dawn) - 007

إِرَمَ ذَاتِ ٱلۡعِمَادِ
በኢረም በባለ ረዣዢሚቱ አዕማድ፡፡

8 - Al-Fajr (The Dawn) - 008

ٱلَّتِي لَمۡ يُخۡلَقۡ مِثۡلُهَا فِي ٱلۡبِلَٰدِ
በዚያች ብጤዋ በአገሮች ውስጥ ያልተፈጠረ በኾነችው፡፡

9 - Al-Fajr (The Dawn) - 009

وَثَمُودَ ٱلَّذِينَ جَابُواْ ٱلصَّخۡرَ بِٱلۡوَادِ
በሰሙድም በእነዚያ በሸለቆው ቋጥኝን የቆረጡ በኾኑት፡፡

10 - Al-Fajr (The Dawn) - 010

وَفِرۡعَوۡنَ ذِي ٱلۡأَوۡتَادِ
በፈርዖንም ባለ ችካሎች በኾነው፡፡

11 - Al-Fajr (The Dawn) - 011

ٱلَّذِينَ طَغَوۡاْ فِي ٱلۡبِلَٰدِ
በእነዚያ በአገሮች ላይ ግፍ የሠሩ፡፡

12 - Al-Fajr (The Dawn) - 012

فَأَكۡثَرُواْ فِيهَا ٱلۡفَسَادَ
በእርሷም ውስጥ ጥፋትን ያበዙ በኾኑት (እንዴት እንደሠራ አታውቅምን?)

13 - Al-Fajr (The Dawn) - 013

فَصَبَّ عَلَيۡهِمۡ رَبُّكَ سَوۡطَ عَذَابٍ
በእነርሱ ላይም ጌታህ የቅጣትን አለንጋ አወረደባቸው፡፡

14 - Al-Fajr (The Dawn) - 014

إِنَّ رَبَّكَ لَبِٱلۡمِرۡصَادِ
ጌታህ በመጠባበቂያ ላይ ነውና፡፡

15 - Al-Fajr (The Dawn) - 015

فَأَمَّا ٱلۡإِنسَٰنُ إِذَا مَا ٱبۡتَلَىٰهُ رَبُّهُۥ فَأَكۡرَمَهُۥ وَنَعَّمَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّيٓ أَكۡرَمَنِ
ሰውማ ጌታው በሞከረው ጊዜ፣ ባከበረውና ባጣቀመውም (ጊዜ) «ጌታዬ አከበረኝ (አበለጠኝ)» ይላል፡፡

16 - Al-Fajr (The Dawn) - 016

وَأَمَّآ إِذَا مَا ٱبۡتَلَىٰهُ فَقَدَرَ عَلَيۡهِ رِزۡقَهُۥ فَيَقُولُ رَبِّيٓ أَهَٰنَنِ
በሞከረውና በእርሱ ላይ ሲሳዩን ባጠበበ ጊዜማ «ጌታዬ አሳነሰኝ» ይላል፡፡

17 - Al-Fajr (The Dawn) - 017

كَلَّاۖ بَل لَّا تُكۡرِمُونَ ٱلۡيَتِيمَ
ይከልከል፤ ይልቁንም የቲምን አታከብሩም፡፡

18 - Al-Fajr (The Dawn) - 018

وَلَا تَحَـٰٓضُّونَ عَلَىٰ طَعَامِ ٱلۡمِسۡكِينِ
ድኻንም በማብላት ላይ አትታዘዙም፡፡

19 - Al-Fajr (The Dawn) - 019

وَتَأۡكُلُونَ ٱلتُّرَاثَ أَكۡلٗا لَّمّٗا
የውርስንም ገንዘብ የመሰብሰብን አበላል ትበላላችሁ፡፡

20 - Al-Fajr (The Dawn) - 020

وَتُحِبُّونَ ٱلۡمَالَ حُبّٗا جَمّٗا
ገንዘብንም ብዙን መውደድ ትወዳላችሁ፡፡

21 - Al-Fajr (The Dawn) - 021

كَلَّآۖ إِذَا دُكَّتِ ٱلۡأَرۡضُ دَكّٗا دَكّٗا
ተዉ፤ ምድር ደጋግማ በተሰባበረች ጊዜ፤

22 - Al-Fajr (The Dawn) - 022

وَجَآءَ رَبُّكَ وَٱلۡمَلَكُ صَفّٗا صَفّٗا
መላእክትም ሰልፍ ሰልፍ ኾነው ጌታህ (ለሱ ክብር በምስማማ መልኩ) በመጣ ጊዜ፤

23 - Al-Fajr (The Dawn) - 023

وَجِاْيٓءَ يَوۡمَئِذِۭ بِجَهَنَّمَۚ يَوۡمَئِذٖ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ وَأَنَّىٰ لَهُ ٱلذِّكۡرَىٰ
ገሀነምም በዚያ ቀን በተመጣች ጊዜ በዚያ ቀን ሰው (ጥፋቱን) ይገነዘባል፡፡ መገንዘብም ለእርሱ ከየቱ?

24 - Al-Fajr (The Dawn) - 024

يَقُولُ يَٰلَيۡتَنِي قَدَّمۡتُ لِحَيَاتِي
«ዋ እኔ! ምነው በሕይወቴ (መልካምን ሥራ) ባስቀደምኩ ኖሮ» ይላል፡፡

25 - Al-Fajr (The Dawn) - 025

فَيَوۡمَئِذٖ لَّا يُعَذِّبُ عَذَابَهُۥٓ أَحَدٞ
በዚያ ቀንም የርሱን አቀጣጥ አንድም አይቀጣም፡፡

26 - Al-Fajr (The Dawn) - 026

وَلَا يُوثِقُ وَثَاقَهُۥٓ أَحَدٞ
የእርሱንም አስተሳሰር አንድም አያስርም፡፡

27 - Al-Fajr (The Dawn) - 027

يَـٰٓأَيَّتُهَا ٱلنَّفۡسُ ٱلۡمُطۡمَئِنَّةُ
(ለአመነች ነፍስም) «አንቺ የረካሺው ነፍስ ሆይ!

28 - Al-Fajr (The Dawn) - 028

ٱرۡجِعِيٓ إِلَىٰ رَبِّكِ رَاضِيَةٗ مَّرۡضِيَّةٗ
«ወዳጅ ተወዳጅ ኾነሽ ወደ ጌታሽ ተመለሺ፡፡

29 - Al-Fajr (The Dawn) - 029

فَٱدۡخُلِي فِي عِبَٰدِي
«በባሮቼም ውስጥ ግቢ፡፡

30 - Al-Fajr (The Dawn) - 030

وَٱدۡخُلِي جَنَّتِي
ገነቴንም ግቢ፤» (ትባላለች)፡፡

Scroll to Top