التكوير

 

At-Takwir

 

The Overthrowing

1 - At-Takwir (The Overthrowing) - 001

إِذَا ٱلشَّمۡسُ كُوِّرَتۡ
ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤

2 - At-Takwir (The Overthrowing) - 002

وَإِذَا ٱلنُّجُومُ ٱنكَدَرَتۡ
ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤

3 - At-Takwir (The Overthrowing) - 003

وَإِذَا ٱلۡجِبَالُ سُيِّرَتۡ
ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤

4 - At-Takwir (The Overthrowing) - 004

وَإِذَا ٱلۡعِشَارُ عُطِّلَتۡ
የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤

5 - At-Takwir (The Overthrowing) - 005

وَإِذَا ٱلۡوُحُوشُ حُشِرَتۡ
እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤

6 - At-Takwir (The Overthrowing) - 006

وَإِذَا ٱلۡبِحَارُ سُجِّرَتۡ
ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤

7 - At-Takwir (The Overthrowing) - 007

وَإِذَا ٱلنُّفُوسُ زُوِّجَتۡ
ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤

8 - At-Takwir (The Overthrowing) - 008

وَإِذَا ٱلۡمَوۡءُۥدَةُ سُئِلَتۡ
በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤

9 - At-Takwir (The Overthrowing) - 009

بِأَيِّ ذَنۢبٖ قُتِلَتۡ
በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤

10 - At-Takwir (The Overthrowing) - 010

وَإِذَا ٱلصُّحُفُ نُشِرَتۡ
ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤

11 - At-Takwir (The Overthrowing) - 011

وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ كُشِطَتۡ
ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤

12 - At-Takwir (The Overthrowing) - 012

وَإِذَا ٱلۡجَحِيمُ سُعِّرَتۡ
ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤

13 - At-Takwir (The Overthrowing) - 013

وَإِذَا ٱلۡجَنَّةُ أُزۡلِفَتۡ
ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤

14 - At-Takwir (The Overthrowing) - 014

عَلِمَتۡ نَفۡسٞ مَّآ أَحۡضَرَتۡ
ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤

15 - At-Takwir (The Overthrowing) - 015

فَلَآ أُقۡسِمُ بِٱلۡخُنَّسِ
ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡

16 - At-Takwir (The Overthrowing) - 016

ٱلۡجَوَارِ ٱلۡكُنَّسِ
ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡

17 - At-Takwir (The Overthrowing) - 017

وَٱلَّيۡلِ إِذَا عَسۡعَسَ
በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤

18 - At-Takwir (The Overthrowing) - 018

وَٱلصُّبۡحِ إِذَا تَنَفَّسَ
በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡

19 - At-Takwir (The Overthrowing) - 019

إِنَّهُۥ لَقَوۡلُ رَسُولٖ كَرِيمٖ
እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡

20 - At-Takwir (The Overthrowing) - 020

ذِي قُوَّةٍ عِندَ ذِي ٱلۡعَرۡشِ مَكِينٖ
የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡

21 - At-Takwir (The Overthrowing) - 021

مُّطَاعٖ ثَمَّ أَمِينٖ
በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡

22 - At-Takwir (The Overthrowing) - 022

وَمَا صَاحِبُكُم بِمَجۡنُونٖ
ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡

23 - At-Takwir (The Overthrowing) - 023

وَلَقَدۡ رَءَاهُ بِٱلۡأُفُقِ ٱلۡمُبِينِ
በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡

24 - At-Takwir (The Overthrowing) - 024

وَمَا هُوَ عَلَى ٱلۡغَيۡبِ بِضَنِينٖ
እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡

25 - At-Takwir (The Overthrowing) - 025

وَمَا هُوَ بِقَوۡلِ شَيۡطَٰنٖ رَّجِيمٖ
እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡

26 - At-Takwir (The Overthrowing) - 026

فَأَيۡنَ تَذۡهَبُونَ
ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?

27 - At-Takwir (The Overthrowing) - 027

إِنۡ هُوَ إِلَّا ذِكۡرٞ لِّلۡعَٰلَمِينَ
እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡

28 - At-Takwir (The Overthrowing) - 028

لِمَن شَآءَ مِنكُمۡ أَن يَسۡتَقِيمَ
ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡

29 - At-Takwir (The Overthrowing) - 029

وَمَا تَشَآءُونَ إِلَّآ أَن يَشَآءَ ٱللَّهُ رَبُّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡

Scroll to Top