الصافات
As-Saffat
Those who set the Ranks
1 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 001
وَٱلصَّـٰٓفَّـٰتِ صَفّٗا
መሰለፍን በሚሰለፉት፡፡
2 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 002
فَٱلزَّـٰجِرَٰتِ زَجۡرٗا
መገሠጽንም በሚገሥጹት፤
3 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 003
فَٱلتَّـٰلِيَٰتِ ذِكۡرًا
ቁርኣንንም በሚያነቡት እምላለሁ፡፡
4 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 004
إِنَّ إِلَٰهَكُمۡ لَوَٰحِدٞ
አምላካችሁ በእርግጥ አንድ ነው፡፡
5 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 005
رَّبُّ ٱلسَّمَٰوَٰتِ وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا بَيۡنَهُمَا وَرَبُّ ٱلۡمَشَٰرِقِ
የሰማያትና የምድር በመካከላቸው ያለውም ፍጡር ሁሉ ጌታ ነው፡፡ የምሥራቆችም ጌታ ነው፡፡
6 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 006
إِنَّا زَيَّنَّا ٱلسَّمَآءَ ٱلدُّنۡيَا بِزِينَةٍ ٱلۡكَوَاكِبِ
እኛ ቅርቢቱን ሰማይ በከዋክብት ጌጥ አጌጥናት፡፡
7 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 007
وَحِفۡظٗا مِّن كُلِّ شَيۡطَٰنٖ مَّارِدٖ
አመጸኛም ከሆነ ሰይጣን ሁሉ መጠበቅን ጠበቅናት፡፡
8 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 008
لَّا يَسَّمَّعُونَ إِلَى ٱلۡمَلَإِ ٱلۡأَعۡلَىٰ وَيُقۡذَفُونَ مِن كُلِّ جَانِبٖ
ወደላይኛው ሰራዊት አያዳምጡም፡፡ ከየወገኑም ሁሉ ችቦ ይጣልባቸዋል፡፡
9 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 009
دُحُورٗاۖ وَلَهُمۡ عَذَابٞ وَاصِبٌ
የሚባረሩ ሲሆኑ (ይጣልባቸዋል)፡፡ ለእነሱም ዘውታሪ ቅጣት አላቸው፡፡
10 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 010
إِلَّا مَنۡ خَطِفَ ٱلۡخَطۡفَةَ فَأَتۡبَعَهُۥ شِهَابٞ ثَاقِبٞ
ንጥቂያን የነጠቀ ወዲያውም አብሪ ኮከብ የተከተለው ሲቀር፤ (እርሱ ይሰማዋል)፡፡
11 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 011
فَٱسۡتَفۡتِهِمۡ أَهُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَم مَّنۡ خَلَقۡنَآۚ إِنَّا خَلَقۡنَٰهُم مِّن طِينٖ لَّازِبِۭ
ጠይቃቸውም፤ እነርሱ በአፈጣጠር ይበልጥ የበረቱ ናቸውን? ወይስ እኛ (ከእነርሱ በፊት) የፈጠርነው? (ፍጡር) እኛ ከሚጣበቅ ጭቃ ፈጠርናቸው፡፡
12 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 012
بَلۡ عَجِبۡتَ وَيَسۡخَرُونَ
ይልቁንም (በማስተባበላቸው) ተደነቅህ፤(ከመደነቅህ) ይሳለቃሉም፡፡
13 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 013
وَإِذَا ذُكِّرُواْ لَا يَذۡكُرُونَ
በተገሠጹም ጊዜ አይመለሱም፡፡
14 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 014
وَإِذَا رَأَوۡاْ ءَايَةٗ يَسۡتَسۡخِرُونَ
ተዓምርን ባዩም ጊዜ ለመሳለቅ ይጠራራሉ፡፡
15 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 015
وَقَالُوٓاْ إِنۡ هَٰذَآ إِلَّا سِحۡرٞ مُّبِينٌ
ይላሉም «ይህ ግልጽ ድግምት እንጂ ሌላ አይደለም፡፡
16 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 016
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَبۡعُوثُونَ
«በሞትንና ዐፈርና አጥንቶችም በኾን ጊዜ እኛ የምንቀሰቀስ ነን?
17 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 017
أَوَءَابَآؤُنَا ٱلۡأَوَّلُونَ
«የቀድሞዎቹ አባቶችንም? (ይላሉ)፡፡
18 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 018
قُلۡ نَعَمۡ وَأَنتُمۡ دَٰخِرُونَ
«አዎን እናንተ ወራዶች ሆናችሁ (ትነሳላችሁ)» በላቸው፡፡
19 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 019
فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ فَإِذَا هُمۡ يَنظُرُونَ
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡ እነርሱም ወዲያውኑ (ምን እንደሚፈጸምባቸው) ያያሉ፡፡
20 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 020
وَقَالُواْ يَٰوَيۡلَنَا هَٰذَا يَوۡمُ ٱلدِّينِ
«ዋ ጥፋታችን! ይህ የፍርዱ ቀን ነው» ይላሉም፡፡
21 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 021
هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
«ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉ የነበራችሁት መለያው ቀን ነው» (ይባላሉ)፡፡
22 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 022
۞ٱحۡشُرُواْ ٱلَّذِينَ ظَلَمُواْ وَأَزۡوَٰجَهُمۡ وَمَا كَانُواْ يَعۡبُدُونَ
(ለመላእክቶችም) «እነዚያን ነፍሶቻቸውን የበደሉትን ሰዎች ጓደኞቻቸውንም ይግገዟቸው የነበሩትንም (ጣዖታት) ሰብስቡ፡፡
23 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 023
مِن دُونِ ٱللَّهِ فَٱهۡدُوهُمۡ إِلَىٰ صِرَٰطِ ٱلۡجَحِيمِ
«ከአላህ ሌላ (የሚገዙዋቸውን ሰብስቧቸው) ወደ እሳት መንገድም ምሩዋቸው፡፡
24 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 024
وَقِفُوهُمۡۖ إِنَّهُم مَّسۡـُٔولُونَ
«አቁሟቸውም፡፡ እነርሱ ተጠያቂዎች ናቸውና» (ይባላል)፡፡
25 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 025
مَا لَكُمۡ لَا تَنَاصَرُونَ
(ለእነርሱም) «የማትረዳዱት ለእናንተ ምን አላችሁ? (ይባላሉ)፡፡
26 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 026
بَلۡ هُمُ ٱلۡيَوۡمَ مُسۡتَسۡلِمُونَ
በእርግጥ እነርሱ ዛሬ እጃቸውን የሰጡ ወራዳዎች ናቸው፡፡
27 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 027
وَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
የሚወቃቀሱም ሆነው ከፊላቸው በከፊሉ ላይ ይመጣሉ፡፡
28 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 028
قَالُوٓاْ إِنَّكُمۡ كُنتُمۡ تَأۡتُونَنَا عَنِ ٱلۡيَمِينِ
(ለአስከታዮቹ) እናንተ ከስተቀኝ ትመጡብን ነበር ይላሉ፡፡
29 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 029
قَالُواْ بَل لَّمۡ تَكُونُواْ مُؤۡمِنِينَ
(አስከታዮቹም) ይላሉ «አይደለም ፈጽሞ ምእምናን አልነበራችሁም፡፡
30 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 030
وَمَا كَانَ لَنَا عَلَيۡكُم مِّن سُلۡطَٰنِۭۖ بَلۡ كُنتُمۡ قَوۡمٗا طَٰغِينَ
«ለእኛም በእናንተ ላይ ምንም ስልጣን አልነበረንም፡፡ በእርግጥ እናንተ ጠማሞች ሕዝቦች ነበራችሁ፡፡
31 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 031
فَحَقَّ عَلَيۡنَا قَوۡلُ رَبِّنَآۖ إِنَّا لَذَآئِقُونَ
«በእኛም ላይ የጌታችን ቃል ተረጋገጠብን፤ እኛ (ሁላችንም ቅጣቱን) ቀማሾች ነን፡፡
32 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 032
فَأَغۡوَيۡنَٰكُمۡ إِنَّا كُنَّا غَٰوِينَ
«ወደ ጥምመት ጠራናችሁም፡፡ እኛ ጠማሞች ነበርንና» (ይላሉ)፡፡
33 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 033
فَإِنَّهُمۡ يَوۡمَئِذٖ فِي ٱلۡعَذَابِ مُشۡتَرِكُونَ
ስለዚህ እነርሱ በዚያ ቀን በቅጣቱ ተጋሪዎች ናቸው፡፡
34 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 034
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ
እኛ በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡
35 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 035
إِنَّهُمۡ كَانُوٓاْ إِذَا قِيلَ لَهُمۡ لَآ إِلَٰهَ إِلَّا ٱللَّهُ يَسۡتَكۡبِرُونَ
እነርሱ ከአላህ ሌላ አምላክ የለም በተባሉ ጊዜ ይኮሩ ነበሩ፡፡
36 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 036
وَيَقُولُونَ أَئِنَّا لَتَارِكُوٓاْ ءَالِهَتِنَا لِشَاعِرٖ مَّجۡنُونِۭ
እኛ ለዕብድ ባለቅኔ ብለን አማልክቶቻችንን የምንተው ነን? ይሉም ነበር፡፡
37 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 037
بَلۡ جَآءَ بِٱلۡحَقِّ وَصَدَّقَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
አይደለም እውነቱን (ሃይማኖት) አመጣ፡፡ መልክተኞቹንም እውነተኛነታቸውን አረጋገጠ፡፡
38 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 038
إِنَّكُمۡ لَذَآئِقُواْ ٱلۡعَذَابِ ٱلۡأَلِيمِ
እናንተ አሳማሚውን ቅጣት በእርግጥ ቀማሾች ናችሁ፡፡
39 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 039
وَمَا تُجۡزَوۡنَ إِلَّا مَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
ትሠሩትም የነበራችሁትን እንጂ ሌላን አትመነዱም፡፡
40 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 040
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ግን ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች (ቅጣትን አይቀምሱም)፡፡
41 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 041
أُوْلَـٰٓئِكَ لَهُمۡ رِزۡقٞ مَّعۡلُومٞ
እነዚያ ለእነርሱ የታወቀ ሲሳይ አላቸው፡፡
42 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 042
فَوَٰكِهُ وَهُم مُّكۡرَمُونَ
ፍራፍሬዎች (አሏቸው) እነርሱም የተከበሩ ናቸው፤
43 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 043
فِي جَنَّـٰتِ ٱلنَّعِيمِ
በድሎት ገነቶች ውስጥ፡፡
44 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 044
عَلَىٰ سُرُرٖ مُّتَقَٰبِلِينَ
ፊት ለፊት የሚታያዩ ሲሆኑ በአልጋዎች ላይ (ይንፈላሰሳሉ)፡፡
45 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 045
يُطَافُ عَلَيۡهِم بِكَأۡسٖ مِّن مَّعِينِۭ
ከሚመነጭ ወይን ጠጅ በያዘ ብርጭቆ በእነርሱ ላይ ይዞርባቸዋል፡፡
46 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 046
بَيۡضَآءَ لَذَّةٖ لِّلشَّـٰرِبِينَ
ነጭ ለጠጪዎች ጣፋጭ ከኾነች፡፡
47 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 047
لَا فِيهَا غَوۡلٞ وَلَا هُمۡ عَنۡهَا يُنزَفُونَ
በእርሷ ውስጥም ምታት የለባትም፡፡ እነርሱም ከእርሷ የሚሰክሩ አይደሉም፡፡
48 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 048
وَعِندَهُمۡ قَٰصِرَٰتُ ٱلطَّرۡفِ عِينٞ
እነርሱም ዘንድ ዓይናቸውን (በባሎቻቸው ላይ) አሳጣሪዎች የኾኑ ዓይናማዎች አልሉ፡፡
49 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 049
كَأَنَّهُنَّ بَيۡضٞ مَّكۡنُونٞ
እነርሱ ልክ የተሸፈነ (የሰጎን) ዕንቁላል ይመስላሉ፡፡
50 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 050
فَأَقۡبَلَ بَعۡضُهُمۡ عَلَىٰ بَعۡضٖ يَتَسَآءَلُونَ
የሚጠያየቁም ሆነው ከፊላቸው ወደ ከፊሉ ይመጣሉ፡፡
51 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 051
قَالَ قَآئِلٞ مِّنۡهُمۡ إِنِّي كَانَ لِي قَرِينٞ
ከእነርሱ የሆነ ተናጋሪ ይላል «እኔ ጓደኛ ነበረኝ፡፡
52 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 052
يَقُولُ أَءِنَّكَ لَمِنَ ٱلۡمُصَدِّقِينَ
«በእርግጥ አንተ ከሚያምኑት ነህን? የሚል፡፡
53 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 053
أَءِذَا مِتۡنَا وَكُنَّا تُرَابٗا وَعِظَٰمًا أَءِنَّا لَمَدِينُونَ
«በሞትንና ዐፈር አጥንቶችም በሆን ጊዜ እኛ በእርግጥ እንመረመራለን?» (የሚል)፡፡
54 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 054
قَالَ هَلۡ أَنتُم مُّطَّلِعُونَ
እናንተ ተመልካቾች ናችሁን? ይላል፡፡
55 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 055
فَٱطَّلَعَ فَرَءَاهُ فِي سَوَآءِ ٱلۡجَحِيمِ
ይመለከታልም፤ በገሀነም መካከልም (ጓደኛውን) ያየዋል፡፡
56 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 056
قَالَ تَٱللَّهِ إِن كِدتَّ لَتُرۡدِينِ
ይላል «በአላህ እምላለሁ፤ በእርግጥ ልታጠፋኝ ቀርበህ ነበር፡፡
57 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 057
وَلَوۡلَا نِعۡمَةُ رَبِّي لَكُنتُ مِنَ ٱلۡمُحۡضَرِينَ
«የጌታየም ጸጋ ባልነበረ ኖሮ ወደ እሳት ከሚቀርቡት እሆን ነበር፡፡»
58 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 058
أَفَمَا نَحۡنُ بِمَيِّتِينَ
(የገነት ሰዎች ይላሉ) «እኛ የምንሞት አይደለንምን?
59 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 059
إِلَّا مَوۡتَتَنَا ٱلۡأُولَىٰ وَمَا نَحۡنُ بِمُعَذَّبِينَ
«የመጀመሪያይቱ መሞታችን ብቻ ስትቀር፡፡ እኛም የምንቅቀጣ አይደለንምን?» (ይላሉ)፡፡
60 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 060
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡفَوۡزُ ٱلۡعَظِيمُ
ይህ (ለገነት ሰዎች የተወሳው) እርሱ በእርግጥ ታላቅ ዕድል ነው፡፡
61 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 061
لِمِثۡلِ هَٰذَا فَلۡيَعۡمَلِ ٱلۡعَٰمِلُونَ
ለዚህ ብጤ ሠሪዎች ይሥሩ፡፡
62 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 062
أَذَٰلِكَ خَيۡرٞ نُّزُلًا أَمۡ شَجَرَةُ ٱلزَّقُّومِ
በመስተንግዶነት ይህ ይበልጣልን? ወይስ የዘቁም ዛፍ?
63 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 063
إِنَّا جَعَلۡنَٰهَا فِتۡنَةٗ لِّلظَّـٰلِمِينَ
እኛ ለበዳዮች ፈተና አድርገናታል፡፡
64 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 064
إِنَّهَا شَجَرَةٞ تَخۡرُجُ فِيٓ أَصۡلِ ٱلۡجَحِيمِ
እርሷ በገሀነም አዘቅት ውስጥ የምትወጣ ዛፍ ናት፡፡
65 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 065
طَلۡعُهَا كَأَنَّهُۥ رُءُوسُ ٱلشَّيَٰطِينِ
እንቡጧ ልክ የሰይጣናት ራሶች ይመስላል፡፡
66 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 066
فَإِنَّهُمۡ لَأٓكِلُونَ مِنۡهَا فَمَالِـُٔونَ مِنۡهَا ٱلۡبُطُونَ
እነርሱም ከእርሷ በይዎች ናቸው፤ ሆዶችንም ከእርሷ ሞይዎች ናቸው፡፡
67 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 067
ثُمَّ إِنَّ لَهُمۡ عَلَيۡهَا لَشَوۡبٗا مِّنۡ حَمِيمٖ
ከዚያም ለእነርሱ በእርሷ ላይ ከተኳሳ ውሃ ቅልቅል (መጠጥ) አልላቸው፡፡
68 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 068
ثُمَّ إِنَّ مَرۡجِعَهُمۡ لَإِلَى ٱلۡجَحِيمِ
ከዚያም መመለሻቸው ወደ ተጋጋመች እሳት ነው፡፡
69 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 069
إِنَّهُمۡ أَلۡفَوۡاْ ءَابَآءَهُمۡ ضَآلِّينَ
እነሱ አባቶቻቸውን የተሳሳቱ ሆነው አግኝተዋልና፡፡
70 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 070
فَهُمۡ عَلَىٰٓ ءَاثَٰرِهِمۡ يُهۡرَعُونَ
እነሱም በፈለጎቻቸው ላይ ይገሰግሳሉና፡፡
71 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 071
وَلَقَدۡ ضَلَّ قَبۡلَهُمۡ أَكۡثَرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
ከእነርሱ በፊትም የቀድሞዎቹ (ሕዝቦች) አብዛኞቻቸው በእርግጥ ተሳስተዋል፡፡
72 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 072
وَلَقَدۡ أَرۡسَلۡنَا فِيهِم مُّنذِرِينَ
በውስጣቸውም አስፈራሪዎችን በእርግጥ ልከናል፡፡
73 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 073
فَٱنظُرۡ كَيۡفَ كَانَ عَٰقِبَةُ ٱلۡمُنذَرِينَ
የተስፈራሪዎቹም መጨረሻ እንዴት እንደነበረ ተመልከት፡፡
74 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 074
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ምርጥ የሆኑት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
75 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 075
وَلَقَدۡ نَادَىٰنَا نُوحٞ فَلَنِعۡمَ ٱلۡمُجِيبُونَ
ኑሕም በእርግጥ ጠራን፡፡ ጥሪውን ተቀባዮቹም ምንኛ አማርን!
76 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 076
وَنَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥ مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
እርሱንም ቤተሰቦቹንም ከከባድ ጭንቅ አዳንን፡፡
77 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 077
وَجَعَلۡنَا ذُرِّيَّتَهُۥ هُمُ ٱلۡبَاقِينَ
ዘሮቹንም እነርሱን ብቻ ቀሪዎች አደረግን፤
78 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 078
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ (መልካም ዝናን) ተውን፡፡
79 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 079
سَلَٰمٌ عَلَىٰ نُوحٖ فِي ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በዓለማት ውስጥ ሰላም በኑሕ ላይ ይኹን፡፡»
80 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 080
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
81 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 081
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ ከምእምናን ባሮቻችን ነውና፡፡
82 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 082
ثُمَّ أَغۡرَقۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አሰጠምን፡፡
83 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 083
۞وَإِنَّ مِن شِيعَتِهِۦ لَإِبۡرَٰهِيمَ
ኢብራሂምም በእርግጥ ከተከታዮቹ ነው፡፡
84 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 084
إِذۡ جَآءَ رَبَّهُۥ بِقَلۡبٖ سَلِيمٍ
ወደ ጌታው በቅን ልብ በመጣ ጊዜ (የኾነውን አስታውስ)፡፡፡
85 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 085
إِذۡ قَالَ لِأَبِيهِ وَقَوۡمِهِۦ مَاذَا تَعۡبُدُونَ
«ለአባቱና ለሕዝቦቹ ምንን ትግገዛላችሁ?» ባለ ጊዜ፡፡
86 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 086
أَئِفۡكًا ءَالِهَةٗ دُونَ ٱللَّهِ تُرِيدُونَ
«ለቅጥፈት ብላችሁ ከአላህ ሌላ አማልክትን ትሻላችሁን?
87 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 087
فَمَا ظَنُّكُم بِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
«በዓለማትም ጌታ ሃሳባችሁ ምንድን ነው?» አለ፡፡
88 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 088
فَنَظَرَ نَظۡرَةٗ فِي ٱلنُّجُومِ
በከዋክብትም መመልከትን ተመለከተ፡፡
89 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 089
فَقَالَ إِنِّي سَقِيمٞ
«እኔ በሽተኛ ነኝም» አለ፡፡
90 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 090
فَتَوَلَّوۡاْ عَنۡهُ مُدۡبِرِينَ
ከእርሱም የሸሹ ሆነው ኼዱ፡፡
91 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 091
فَرَاغَ إِلَىٰٓ ءَالِهَتِهِمۡ فَقَالَ أَلَا تَأۡكُلُونَ
ወደ አማልክቶቻቸውም ተዘነበለ፡፡ አለም፡- «አትበሉምን?»
92 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 092
مَا لَكُمۡ لَا تَنطِقُونَ
«የማትናገሩት ለናንተ ምን አላችሁ?»
93 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 093
فَرَاغَ عَلَيۡهِمۡ ضَرۡبَۢا بِٱلۡيَمِينِ
በኀይል የሚመታቸውም ሆኖ በእነርሱ ላይ በድብቅ ተዘነበለ፡፡
94 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 094
فَأَقۡبَلُوٓاْ إِلَيۡهِ يَزِفُّونَ
ወደእርሱም (ሰዎቹ) እየሮጡ መጡ፡፡
95 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 095
قَالَ أَتَعۡبُدُونَ مَا تَنۡحِتُونَ
አላቸው «የምትጠርቡትን ትግገዛላችሁን?»
96 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 096
وَٱللَّهُ خَلَقَكُمۡ وَمَا تَعۡمَلُونَ
«አላህ እናንተንም የምትሠሩትንም የፈጠረ ሲኾን፡፡»
97 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 097
قَالُواْ ٱبۡنُواْ لَهُۥ بُنۡيَٰنٗا فَأَلۡقُوهُ فِي ٱلۡجَحِيمِ
«ለእርሱም ግንብን ገንቡ በእሳት ነበልባል ውስጥ ጣሉትም» አሉ፡፡
98 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 098
فَأَرَادُواْ بِهِۦ كَيۡدٗا فَجَعَلۡنَٰهُمُ ٱلۡأَسۡفَلِينَ
በእርሱም ተንኮልን አሰቡ፡፡ ዝቅተኞችም አደረግናቸው፡፡
99 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 099
وَقَالَ إِنِّي ذَاهِبٌ إِلَىٰ رَبِّي سَيَهۡدِينِ
አለም «እኔ ወደ ጌታዬ ኼያጅ ነኝ፡፡ በእርግጥ ይመራኛልና፡፡»
100 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 100
رَبِّ هَبۡ لِي مِنَ ٱلصَّـٰلِحِينَ
ጌታዬ ሆይ! ከመልካሞቹ የሆነን (ልጅ) ስጠኝ፡፡
101 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 101
فَبَشَّرۡنَٰهُ بِغُلَٰمٍ حَلِيمٖ
ታጋሽ በሆነ ወጣት ልጅም አበሰርነው፡፡
102 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 102
فَلَمَّا بَلَغَ مَعَهُ ٱلسَّعۡيَ قَالَ يَٰبُنَيَّ إِنِّيٓ أَرَىٰ فِي ٱلۡمَنَامِ أَنِّيٓ أَذۡبَحُكَ فَٱنظُرۡ مَاذَا تَرَىٰۚ قَالَ يَـٰٓأَبَتِ ٱفۡعَلۡ مَا تُؤۡمَرُۖ سَتَجِدُنِيٓ إِن شَآءَ ٱللَّهُ مِنَ ٱلصَّـٰبِرِينَ
ከእርሱ ጋርም ለሥራ በደረሰ ጊዜ «ልጄ ሆይ! እኔ በሕልሜ እኔ የማርድህ ሆኜ አያለሁ፡፡ ተመልከትም፤ ምን ታያለህ?» አለው፡፡ «አባቴ ሆይ! የታዘዝከውን ሥራ፡፡ አላህ ቢሻ ከታጋሾቹ ሆኜ ታገኘኛለህ» አለ፡፡
103 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 103
فَلَمَّآ أَسۡلَمَا وَتَلَّهُۥ لِلۡجَبِينِ
ሁለቱም ትዕዛዙን በተቀበሉና በግንባሩም ጎን ላይ በጣለው ጊዜ (የሆነው ሆነ)፡፡
104 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 104
وَنَٰدَيۡنَٰهُ أَن يَـٰٓإِبۡرَٰهِيمُ
ጠራነውም፤ (አልነው) «ኢብራሂም ሆይ!
105 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 105
قَدۡ صَدَّقۡتَ ٱلرُّءۡيَآۚ إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
ራእይቱን በእውነት አረጋገጥክ፡፡» እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
106 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 106
إِنَّ هَٰذَا لَهُوَ ٱلۡبَلَـٰٓؤُاْ ٱلۡمُبِينُ
ይህ እርሱ በእውነት ግልጽ ፈተና ነው፡፡
107 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 107
وَفَدَيۡنَٰهُ بِذِبۡحٍ عَظِيمٖ
በታላቅ ዕርድም (መስዋዕት) ተቤዠነው፡፡
108 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 108
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በእርሱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን አስቀረንለት፡፡
109 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 109
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِبۡرَٰهِيمَ
ሰላም በኢብራሂም ላይ ይሁን፡፡
110 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 110
كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
111 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 111
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ በእርግጥ ካመኑት ባሮቻችን ነው፡፡
112 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 112
وَبَشَّرۡنَٰهُ بِإِسۡحَٰقَ نَبِيّٗا مِّنَ ٱلصَّـٰلِحِينَ
በኢስሐቅም አበሰርነው፡፡ ከመልካሞቹ የሆነ ነቢይ ሲሆን፡፡
113 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 113
وَبَٰرَكۡنَا عَلَيۡهِ وَعَلَىٰٓ إِسۡحَٰقَۚ وَمِن ذُرِّيَّتِهِمَا مُحۡسِنٞ وَظَالِمٞ لِّنَفۡسِهِۦ مُبِينٞ
በእርሱና በኢስሐቅ ላይም ባረክን፡፡ ከሁለቱም ዘሮች በጎ ሠሪ አልለ፡፡ ለነፍሱ ግልጽ በዳይም አለ፡፡
114 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 114
وَلَقَدۡ مَنَنَّا عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
በሙሳና በሃሩን ላይም በእርግጥ ለገስን፡፡
115 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 115
وَنَجَّيۡنَٰهُمَا وَقَوۡمَهُمَا مِنَ ٱلۡكَرۡبِ ٱلۡعَظِيمِ
እነርሱንም ሕዝቦቻቸውንም ከታላቅ ጭንቅ አዳንን፡፡
116 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 116
وَنَصَرۡنَٰهُمۡ فَكَانُواْ هُمُ ٱلۡغَٰلِبِينَ
ረዳናቸውም፡፡ እነርሱም አሸናፊዎች ነበሩ፡፡
117 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 117
وَءَاتَيۡنَٰهُمَا ٱلۡكِتَٰبَ ٱلۡمُسۡتَبِينَ
በጣም የተብራራውንም መጽሐፍ ሰጠናቸው፡፡
118 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 118
وَهَدَيۡنَٰهُمَا ٱلصِّرَٰطَ ٱلۡمُسۡتَقِيمَ
ቀጥተኛውንም መንገድ መራናቸው፡፡
119 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 119
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِمَا فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በሁለቱም ላይ በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንላቸው፡፡
120 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 120
سَلَٰمٌ عَلَىٰ مُوسَىٰ وَهَٰرُونَ
ሰላም በሙሳና በሃሩን ላይ ይሁን፡፡
121 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 121
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ በጎ አድራጊዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡
122 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 122
إِنَّهُمَا مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
ሁለቱም በእርግጥ ከአመኑት ባሮቻችን ናቸው፡፡
123 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 123
وَإِنَّ إِلۡيَاسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ኢልያስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
124 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 124
إِذۡ قَالَ لِقَوۡمِهِۦٓ أَلَا تَتَّقُونَ
ለሕዝቦቹ ባለ ጊዜ (አስታውስ)፤ አላህን አትፈሩምን?
125 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 125
أَتَدۡعُونَ بَعۡلٗا وَتَذَرُونَ أَحۡسَنَ ٱلۡخَٰلِقِينَ
በዕልን ትገዛላችሁን? ከሰዓሊዎቹ ሁሉ ይበልጥ በጣም አሳማሪ የሆነውንም አምላክ ትተዋላችሁን?
126 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 126
ٱللَّهَ رَبَّكُمۡ وَرَبَّ ءَابَآئِكُمُ ٱلۡأَوَّلِينَ
አላህን ጌታችሁንና የቀድሞዎቹ አባቶቻችሁን ጌታ (ትተዋላችሁን)?
127 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 127
فَكَذَّبُوهُ فَإِنَّهُمۡ لَمُحۡضَرُونَ
አስተባበሉትም፡፡ ስለዚህ እነርሱ (ለቅጣት) የሚጣዱ ናቸው፡፡
128 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 128
إِلَّا عِبَادَ ٱللَّهِ ٱلۡمُخۡلَصِينَ
ንጹሕ የተደረጉት የአላህ ባሮች ብቻ ሲቀሩ፡፡
129 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 129
وَتَرَكۡنَا عَلَيۡهِ فِي ٱلۡأٓخِرِينَ
በእርሱ ላይም በኋለኞቹ ሕዝቦች ውስጥ መልካም ዝናን ተውንለት፡፡
130 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 130
سَلَٰمٌ عَلَىٰٓ إِلۡ يَاسِينَ
ሰላም በኢልያሲን ላይ ይሁን፡፡
131 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 131
إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን እንመነዳለን፡፡
132 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 132
إِنَّهُۥ مِنۡ عِبَادِنَا ٱلۡمُؤۡمِنِينَ
እርሱ በእርግጥ ከምእመናን ባሮቻችን ነው፡፡
133 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 133
وَإِنَّ لُوطٗا لَّمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ሉጥም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
134 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 134
إِذۡ نَجَّيۡنَٰهُ وَأَهۡلَهُۥٓ أَجۡمَعِينَ
እርሱንና ቤተሰቦቹን ሁሉንም በአዳንናቸው ጊዜ (አስታውስ)፡፡
135 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 135
إِلَّا عَجُوزٗا فِي ٱلۡغَٰبِرِينَ
(በቅጣቱ ውስጥ) ከቀሪዎቹ የሆነችው አሮጊት ብቻ ስትቀር፡፡
136 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 136
ثُمَّ دَمَّرۡنَا ٱلۡأٓخَرِينَ
ከዚያም ሌሎቹን አጠፋን፡፡
137 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 137
وَإِنَّكُمۡ لَتَمُرُّونَ عَلَيۡهِم مُّصۡبِحِينَ
እናንተም ያነጋችሁ ስትሆኑ በእነርሱ (መኖሪያዎች) ላይ (በቀን) ታልፋላችሁ፡፡
138 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 138
وَبِٱلَّيۡلِۚ أَفَلَا تَعۡقِلُونَ
በሌሊትም (ታልፋላችሁ)፤ ልብም አታደርጉምን?
139 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 139
وَإِنَّ يُونُسَ لَمِنَ ٱلۡمُرۡسَلِينَ
ዩኑስም በእርግጥ ከመልክተኞቹ ነው፡፡
140 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 140
إِذۡ أَبَقَ إِلَى ٱلۡفُلۡكِ ٱلۡمَشۡحُونِ
ወደ ተመላው መርከብ በኮበለለ ጊዜ (አስታውስ)፡፡
141 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 141
فَسَاهَمَ فَكَانَ مِنَ ٱلۡمُدۡحَضِينَ
ዕጣም ተጣጣለ፡፡ ከተሸነፉትም ሆነ፡፡
142 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 142
فَٱلۡتَقَمَهُ ٱلۡحُوتُ وَهُوَ مُلِيمٞ
እርሱም ተወቃሽ ሲሆን ዐሳው ዋጠው፡፡
143 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 143
فَلَوۡلَآ أَنَّهُۥ كَانَ مِنَ ٱلۡمُسَبِّحِينَ
እርሱ ለጌታው ከአወዳሾቹ ባልሆነም ኖሮ፤
144 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 144
لَلَبِثَ فِي بَطۡنِهِۦٓ إِلَىٰ يَوۡمِ يُبۡعَثُونَ
እስከሚቀሰቀሱበት ቀን ድረስ በሆዱ ውስጥ በቆየ ነበር፡፡
145 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 145
۞فَنَبَذۡنَٰهُ بِٱلۡعَرَآءِ وَهُوَ سَقِيمٞ
እርሱ በሽተኛ ሆኖ በቃይ በሌለው (በባሕር) ዳርቻ ላይ ጣልነውም፡፡
146 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 146
وَأَنۢبَتۡنَا عَلَيۡهِ شَجَرَةٗ مِّن يَقۡطِينٖ
በእርሱም ላይ (በአጠገቡ) ከቅል የሆነችን ዛፍ አበቀልን፡፡
147 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 147
وَأَرۡسَلۡنَٰهُ إِلَىٰ مِاْئَةِ أَلۡفٍ أَوۡ يَزِيدُونَ
ወደ መቶ ሺሕ ሰዎችም (ዳግመኛ) ላክነው፡፡ ከቶውንም ይጨምራሉ።
148 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 148
فَـَٔامَنُواْ فَمَتَّعۡنَٰهُمۡ إِلَىٰ حِينٖ
አመኑም፡፡ እስከ ጊዜ ድረስም አጣቀምናቸው፡፡
149 - As-Saffat (Those who set the Ranks) - 149