الضحى

 

Ad-Duhaa

 

The Morning Hours

1 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 001

وَٱلضُّحَىٰ
በረፋዱ እምላለሁ፡፡

2 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 002

وَٱلَّيۡلِ إِذَا سَجَىٰ
በሌሊቱም ጸጥ ባለ ጊዜ፤

3 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 003

مَا وَدَّعَكَ رَبُّكَ وَمَا قَلَىٰ
ጌታህ አላሰናበተህም፤ አልጠላህምም፡፡

4 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 004

وَلَلۡأٓخِرَةُ خَيۡرٞ لَّكَ مِنَ ٱلۡأُولَىٰ
መጨረሻይቱም (ዓለም) ከመጀመሪያይቱ ይልቅ ላንተ በላጭ ናት፡፡

5 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 005

وَلَسَوۡفَ يُعۡطِيكَ رَبُّكَ فَتَرۡضَىٰٓ
ጌታህም ወደ ፊት (ብዙን ስጦታ) በእርግጥ ይሰጥሃል፡፡ ትደሰታለህም፡፡

6 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 006

أَلَمۡ يَجِدۡكَ يَتِيمٗا فَـَٔاوَىٰ
የቲም ኾነህ አላገኘህምና አላስጠጋህምን? (አስጠግቶሃል)፡፡

7 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 007

وَوَجَدَكَ ضَآلّٗا فَهَدَىٰ
የሳትክም ኾነህ አገኘህ መራህም፡፡

8 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 008

وَوَجَدَكَ عَآئِلٗا فَأَغۡنَىٰ
ድኻም ኾነህ አገኘህ፤ አከበረህም፡፡

9 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 009

فَأَمَّا ٱلۡيَتِيمَ فَلَا تَقۡهَرۡ
የቲምንማ አትጨቁን፡፡

10 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 010

وَأَمَّا ٱلسَّآئِلَ فَلَا تَنۡهَرۡ
ለማኝንም አትገላምጥ፡፡

11 - Ad-Duhaa (The Morning Hours) - 011

وَأَمَّا بِنِعۡمَةِ رَبِّكَ فَحَدِّثۡ
በጌታህም ጸጋ አውራ፤ (ግለጻት)፡፡

Scroll to Top