الليل
Al-Layl
The Night
1 - Al-Layl (The Night) - 001
وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰ
በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡
2 - Al-Layl (The Night) - 002
وَٱلنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ
በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡
3 - Al-Layl (The Night) - 003
وَمَا خَلَقَ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ
ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡
4 - Al-Layl (The Night) - 004
إِنَّ سَعۡيَكُمۡ لَشَتَّىٰ
ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡
5 - Al-Layl (The Night) - 005
فَأَمَّا مَنۡ أَعۡطَىٰ وَٱتَّقَىٰ
የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡
6 - Al-Layl (The Night) - 006
وَصَدَّقَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ
በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤
7 - Al-Layl (The Night) - 007
فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡيُسۡرَىٰ
ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
8 - Al-Layl (The Night) - 008
وَأَمَّا مَنۢ بَخِلَ وَٱسۡتَغۡنَىٰ
የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤
9 - Al-Layl (The Night) - 009
وَكَذَّبَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ
በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤
10 - Al-Layl (The Night) - 010
فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡعُسۡرَىٰ
ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
11 - Al-Layl (The Night) - 011
وَمَا يُغۡنِي عَنۡهُ مَالُهُۥٓ إِذَا تَرَدَّىٰٓ
በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡
12 - Al-Layl (The Night) - 012
إِنَّ عَلَيۡنَا لَلۡهُدَىٰ
ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡
13 - Al-Layl (The Night) - 013
وَإِنَّ لَنَا لَلۡأٓخِرَةَ وَٱلۡأُولَىٰ
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡
14 - Al-Layl (The Night) - 014
فَأَنذَرۡتُكُمۡ نَارٗا تَلَظَّىٰ
የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡
15 - Al-Layl (The Night) - 015
لَا يَصۡلَىٰهَآ إِلَّا ٱلۡأَشۡقَى
ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡
16 - Al-Layl (The Night) - 016
ٱلَّذِي كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡
17 - Al-Layl (The Night) - 017
وَسَيُجَنَّبُهَا ٱلۡأَتۡقَى
አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡
18 - Al-Layl (The Night) - 018
ٱلَّذِي يُؤۡتِي مَالَهُۥ يَتَزَكَّىٰ
ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡
19 - Al-Layl (The Night) - 019
وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعۡمَةٖ تُجۡزَىٰٓ
ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡
20 - Al-Layl (The Night) - 020
إِلَّا ٱبۡتِغَآءَ وَجۡهِ رَبِّهِ ٱلۡأَعۡلَىٰ
ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡
21 - Al-Layl (The Night) - 021