الشمس

 

Ash-Shams

 

The Sun

1 - Ash-Shams (The Sun) - 001

وَٱلشَّمۡسِ وَضُحَىٰهَا
በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡

2 - Ash-Shams (The Sun) - 002

وَٱلۡقَمَرِ إِذَا تَلَىٰهَا
በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤

3 - Ash-Shams (The Sun) - 003

وَٱلنَّهَارِ إِذَا جَلَّىٰهَا
በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤

4 - Ash-Shams (The Sun) - 004

وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰهَا
በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤

5 - Ash-Shams (The Sun) - 005

وَٱلسَّمَآءِ وَمَا بَنَىٰهَا
በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤

6 - Ash-Shams (The Sun) - 006

وَٱلۡأَرۡضِ وَمَا طَحَىٰهَا
በምድሪቱም በዘረጋትም፤

7 - Ash-Shams (The Sun) - 007

وَنَفۡسٖ وَمَا سَوَّىٰهَا
በነፍስም ባስተካከላትም፤

8 - Ash-Shams (The Sun) - 008

فَأَلۡهَمَهَا فُجُورَهَا وَتَقۡوَىٰهَا
አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡

9 - Ash-Shams (The Sun) - 009

قَدۡ أَفۡلَحَ مَن زَكَّىٰهَا
(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡

10 - Ash-Shams (The Sun) - 010

وَقَدۡ خَابَ مَن دَسَّىٰهَا
(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡

11 - Ash-Shams (The Sun) - 011

كَذَّبَتۡ ثَمُودُ بِطَغۡوَىٰهَآ
ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡

12 - Ash-Shams (The Sun) - 012

إِذِ ٱنۢبَعَثَ أَشۡقَىٰهَا
ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡

13 - Ash-Shams (The Sun) - 013

فَقَالَ لَهُمۡ رَسُولُ ٱللَّهِ نَاقَةَ ٱللَّهِ وَسُقۡيَٰهَا
ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡

14 - Ash-Shams (The Sun) - 014

فَكَذَّبُوهُ فَعَقَرُوهَا فَدَمۡدَمَ عَلَيۡهِمۡ رَبُّهُم بِذَنۢبِهِمۡ فَسَوَّىٰهَا
አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡

15 - Ash-Shams (The Sun) - 015

وَلَا يَخَافُ عُقۡبَٰهَا
ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አይፈራም፡፡

Scroll to Top