المطففين

 

Al-Mutaffifin

 

The Defrauding

1 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 001

وَيۡلٞ لِّلۡمُطَفِّفِينَ
ለሰላቢዎች ወዮላቸው፡፡

2 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 002

ٱلَّذِينَ إِذَا ٱكۡتَالُواْ عَلَى ٱلنَّاسِ يَسۡتَوۡفُونَ
ለእነዚያ ከሰዎች ባስሰፈሩ ጊዜ የሚያስሞሉ፡፡

3 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 003

وَإِذَا كَالُوهُمۡ أَو وَّزَنُوهُمۡ يُخۡسِرُونَ
ለእነርሱም (ለሰዎቹ) በሰፈሩ ወይም በመዘኑላቸው ጊዜ የሚያጎድሉ (ለኾኑት)፡፡

4 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 004

أَلَا يَظُنُّ أُوْلَـٰٓئِكَ أَنَّهُم مَّبۡعُوثُونَ
እነዚያ እነርሱ ተቀስቃሾች መኾናቸውን አያውቁምን?

5 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 005

لِيَوۡمٍ عَظِيمٖ
በታላቁ ቀን፡፡

6 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 006

يَوۡمَ يَقُومُ ٱلنَّاسُ لِرَبِّ ٱلۡعَٰلَمِينَ
ሰዎች ሁሉ ለዓለማት ጌታ (ፍርድ)፤ በሚቆሙበት ቀን (ተቀስቃሾች መኾናቸውን)፡፡

7 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 007

كَلَّآ إِنَّ كِتَٰبَ ٱلۡفُجَّارِ لَفِي سِجِّينٖ
በእውነት የከሓዲዎቹ (የሰላቢዎቹ) መጽሐፍ በእርግጥ በሲጂን ውስጥ ነው፡፡

8 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 008

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا سِجِّينٞ
ሲጂንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

9 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 009

كِتَٰبٞ مَّرۡقُومٞ
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡

10 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 010

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

11 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 011

ٱلَّذِينَ يُكَذِّبُونَ بِيَوۡمِ ٱلدِّينِ
ለእነዚያ በፍርዱ ቀን ለሚያስተባብሉት፡፡

12 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 012

وَمَا يُكَذِّبُ بِهِۦٓ إِلَّا كُلُّ مُعۡتَدٍ أَثِيمٍ
በእርሱም ወሰን አላፊ ኀጢአተኛ ሁሉ እንጅ ሌላ አያስተባብልም፡፡

13 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 013

إِذَا تُتۡلَىٰ عَلَيۡهِ ءَايَٰتُنَا قَالَ أَسَٰطِيرُ ٱلۡأَوَّلِينَ
አንቀጾቻችን በእርሱ ላይ በተነበቡ ጊዜ «የመጀመሪያዎቹ ሰዎች ተረቶች ናቸው» ይላል፡፡

14 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 014

كَلَّاۖ بَلۡۜ رَانَ عَلَىٰ قُلُوبِهِم مَّا كَانُواْ يَكۡسِبُونَ
ይከልከል፤ ይልቁንም በልቦቻቸው ላይ ይሠሩት የነበሩት (ኀጢአት) ደገደገባቸው፡፡

15 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 015

كَلَّآ إِنَّهُمۡ عَن رَّبِّهِمۡ يَوۡمَئِذٖ لَّمَحۡجُوبُونَ
ይከልከሉ፤ እነርሱ በዚያ ቀን ከጌታቸው (ማየት) ተጋራጆች ናቸው፡፡

16 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 016

ثُمَّ إِنَّهُمۡ لَصَالُواْ ٱلۡجَحِيمِ
ከዚያም እነርሱ በእርግጥ ገሀነምን ገቢዎች ናቸው፡፡

17 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 017

ثُمَّ يُقَالُ هَٰذَا ٱلَّذِي كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
ከዚያም «ይህ ያ በእርሱ ታስተባብሉበት የነበራችሁት ነው» ይባላሉ፡፡

18 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 018

كَلَّآ إِنَّ كِتَٰبَ ٱلۡأَبۡرَارِ لَفِي عِلِّيِّينَ
በእውነቱ የእውነተኞቹ ምእምናን መጽሐፍ በዒሊዮን ውስጥ ነው፡፡

19 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 019

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا عِلِّيُّونَ
ዒሊዮንም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?

20 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 020

كِتَٰبٞ مَّرۡقُومٞ
የታተመ መጽሐፍ ነው፡፡

21 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 021

يَشۡهَدُهُ ٱلۡمُقَرَّبُونَ
ባለሟልዎቹ ይጣዱታል፡፡

22 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 022

إِنَّ ٱلۡأَبۡرَارَ لَفِي نَعِيمٍ
እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በድሎት (ገነት) ውስጥ ናቸው፡፡

23 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 023

عَلَى ٱلۡأَرَآئِكِ يَنظُرُونَ
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው ይመለከታሉ፡፡

24 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 024

تَعۡرِفُ فِي وُجُوهِهِمۡ نَضۡرَةَ ٱلنَّعِيمِ
በፊቶቻቸው ላይ የድሎትን ውበት ታውቃለህ፡፡

25 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 025

يُسۡقَوۡنَ مِن رَّحِيقٖ مَّخۡتُومٍ
ተጣርቶ ከታተመ ጠጅ ይጠጣሉ፡፡

26 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 026

خِتَٰمُهُۥ مِسۡكٞۚ وَفِي ذَٰلِكَ فَلۡيَتَنَافَسِ ٱلۡمُتَنَٰفِسُونَ
ማተሚያው ምስክ ከኾነ፤ በዚህም ተሽቀዳዳሚዎች ይሽቀዳደሙ፡፡

27 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 027

وَمِزَاجُهُۥ مِن تَسۡنِيمٍ
መበረዣውም ከተስኒም ነው፡፡

28 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 028

عَيۡنٗا يَشۡرَبُ بِهَا ٱلۡمُقَرَّبُونَ
ባለሟሎቹ ከእርሷ የሚጠጡላት ምንጭ ናት፡፡

29 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 029

إِنَّ ٱلَّذِينَ أَجۡرَمُواْ كَانُواْ مِنَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ يَضۡحَكُونَ
እነዚያ ያምመጹት በእነዚያ ባመኑት በእርግጥ ይስቁ ነበሩ፡፡

30 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 030

وَإِذَا مَرُّواْ بِهِمۡ يَتَغَامَزُونَ
በእነርሱም ላይ ባለፉ ጊዜ ይጠቃቀሱ ነበር፡፡

31 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 031

وَإِذَا ٱنقَلَبُوٓاْ إِلَىٰٓ أَهۡلِهِمُ ٱنقَلَبُواْ فَكِهِينَ
ወደ ቤተሰቦቻቸውም በተመለሱ ጊዜ (በመሳለቃቸው) ተደሳቾች ኾነው ይመለሱ ነበር፡፡

32 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 032

وَإِذَا رَأَوۡهُمۡ قَالُوٓاْ إِنَّ هَـٰٓؤُلَآءِ لَضَآلُّونَ
ባዩዋቸውም ጊዜ «እነዚህ በእርግጥ ተሳሳቾች ናቸው» ይሉ ነበር፡፡

33 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 033

وَمَآ أُرۡسِلُواْ عَلَيۡهِمۡ حَٰفِظِينَ
በነርሱ ላይ ተጠባባቂዎች ተደርገው ያልተላኩ ሲኾኑ፡፡

34 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 034

فَٱلۡيَوۡمَ ٱلَّذِينَ ءَامَنُواْ مِنَ ٱلۡكُفَّارِ يَضۡحَكُونَ
ዛሬ (በትንሣኤ ቀን) እነዚያ ያመኑት በከሓዲዎቹ ይስቃሉ፡፡

35 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 035

عَلَى ٱلۡأَرَآئِكِ يَنظُرُونَ
በባለ አጎበር አልጋዎች ላይ ኾነው የሚመለከቱ ሲኾኑ (ይስቃሉ)፡፡

36 - Al-Mutaffifin (The Defrauding) - 036

هَلۡ ثُوِّبَ ٱلۡكُفَّارُ مَا كَانُواْ يَفۡعَلُونَ
ከሓዲዎች ይሠሩት የነበሩትን (ዋጋ) ተመነዱን? (ይላሉ)፡፡

Scroll to Top