عبس
'Abasa
He Frowned
1 - 'Abasa (He Frowned) - 001
عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡
2 - 'Abasa (He Frowned) - 002
أَن جَآءَهُ ٱلۡأَعۡمَىٰ
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡
3 - 'Abasa (He Frowned) - 003
وَمَا يُدۡرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡
4 - 'Abasa (He Frowned) - 004
أَوۡ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكۡرَىٰٓ
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡
5 - 'Abasa (He Frowned) - 005
أَمَّا مَنِ ٱسۡتَغۡنَىٰ
የተብቃቃው ሰውማ፤
6 - 'Abasa (He Frowned) - 006
فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡
7 - 'Abasa (He Frowned) - 007
وَمَا عَلَيۡكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡
8 - 'Abasa (He Frowned) - 008
وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسۡعَىٰ
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤
9 - 'Abasa (He Frowned) - 009
وَهُوَ يَخۡشَىٰ
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤
10 - 'Abasa (He Frowned) - 010
فَأَنتَ عَنۡهُ تَلَهَّىٰ
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡
11 - 'Abasa (He Frowned) - 011
كَلَّآ إِنَّهَا تَذۡكِرَةٞ
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡
12 - 'Abasa (He Frowned) - 012
فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡
13 - 'Abasa (He Frowned) - 013
فِي صُحُفٖ مُّكَرَّمَةٖ
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡
14 - 'Abasa (He Frowned) - 014
مَّرۡفُوعَةٖ مُّطَهَّرَةِۭ
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡
15 - 'Abasa (He Frowned) - 015
بِأَيۡدِي سَفَرَةٖ
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡
16 - 'Abasa (He Frowned) - 016
كِرَامِۭ بَرَرَةٖ
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡
17 - 'Abasa (He Frowned) - 017
قُتِلَ ٱلۡإِنسَٰنُ مَآ أَكۡفَرَهُۥ
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?
18 - 'Abasa (He Frowned) - 018
مِنۡ أَيِّ شَيۡءٍ خَلَقَهُۥ
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)
19 - 'Abasa (He Frowned) - 019
مِن نُّطۡفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡
20 - 'Abasa (He Frowned) - 020
ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡
21 - 'Abasa (He Frowned) - 021
ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقۡبَرَهُۥ
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡
22 - 'Abasa (He Frowned) - 022
ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡
23 - 'Abasa (He Frowned) - 023
كَلَّا لَمَّا يَقۡضِ مَآ أَمَرَهُۥ
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡
24 - 'Abasa (He Frowned) - 024
فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ
ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡
25 - 'Abasa (He Frowned) - 025
أَنَّا صَبَبۡنَا ٱلۡمَآءَ صَبّٗا
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡
26 - 'Abasa (He Frowned) - 026
ثُمَّ شَقَقۡنَا ٱلۡأَرۡضَ شَقّٗا
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤
27 - 'Abasa (He Frowned) - 027
فَأَنۢبَتۡنَا فِيهَا حَبّٗا
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤
28 - 'Abasa (He Frowned) - 028
وَعِنَبٗا وَقَضۡبٗا
ወይንንም፤ እርጥብ (ያበቀልን)፤
29 - 'Abasa (He Frowned) - 029
وَزَيۡتُونٗا وَنَخۡلٗا
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤
30 - 'Abasa (He Frowned) - 030
وَحَدَآئِقَ غُلۡبٗا
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤
31 - 'Abasa (He Frowned) - 031
وَفَٰكِهَةٗ وَأَبّٗا
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡
32 - 'Abasa (He Frowned) - 032
مَّتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡
33 - 'Abasa (He Frowned) - 033
فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤
34 - 'Abasa (He Frowned) - 034
يَوۡمَ يَفِرُّ ٱلۡمَرۡءُ مِنۡ أَخِيهِ
ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤
35 - 'Abasa (He Frowned) - 035
وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ
ከናቱም ካባቱም፤
36 - 'Abasa (He Frowned) - 036
وَصَٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ
ከሚስቱም ከልጁም፤
37 - 'Abasa (He Frowned) - 037
لِكُلِّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ يَوۡمَئِذٖ شَأۡنٞ يُغۡنِيهِ
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡
38 - 'Abasa (He Frowned) - 038
وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ مُّسۡفِرَةٞ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤
39 - 'Abasa (He Frowned) - 039
ضَاحِكَةٞ مُّسۡتَبۡشِرَةٞ
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡
40 - 'Abasa (He Frowned) - 040
وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذٍ عَلَيۡهَا غَبَرَةٞ
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤
41 - 'Abasa (He Frowned) - 041
تَرۡهَقُهَا قَتَرَةٌ
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤
42 - 'Abasa (He Frowned) - 042