عبس

 

'Abasa

 

He Frowned

1 - 'Abasa (He Frowned) - 001

عَبَسَ وَتَوَلَّىٰٓ
ፊቱን አጨፈገገ፤ ዞረም፡፡

2 - 'Abasa (He Frowned) - 002

أَن جَآءَهُ ٱلۡأَعۡمَىٰ
ዕውሩ ስለ መጣው፡፡

3 - 'Abasa (He Frowned) - 003

وَمَا يُدۡرِيكَ لَعَلَّهُۥ يَزَّكَّىٰٓ
ምን ያሳውቅሃል? (ከኀጢአቶቹ) ሊጥራራ ይከጀላል፡፡

4 - 'Abasa (He Frowned) - 004

أَوۡ يَذَّكَّرُ فَتَنفَعَهُ ٱلذِّكۡرَىٰٓ
ወይም ሊገሠጽ ግሠጼይቱም ልትጠቅመው (ይከጀላል)፡፡

5 - 'Abasa (He Frowned) - 005

أَمَّا مَنِ ٱسۡتَغۡنَىٰ
የተብቃቃው ሰውማ፤

6 - 'Abasa (He Frowned) - 006

فَأَنتَ لَهُۥ تَصَدَّىٰ
አንተ ለእርሱ (ለእምነቱ በመጓጓት) በፈገግታ ትቀበለዋለህ፡፡

7 - 'Abasa (He Frowned) - 007

وَمَا عَلَيۡكَ أَلَّا يَزَّكَّىٰ
ባይጥራራ (ባያምን) ባንተ ላይ ምንም የሌለብህ ስትኾን፡፡

8 - 'Abasa (He Frowned) - 008

وَأَمَّا مَن جَآءَكَ يَسۡعَىٰ
እየገሰገሰ የመጣህ ሰውማ፤

9 - 'Abasa (He Frowned) - 009

وَهُوَ يَخۡشَىٰ
እርሱ (አላህን) የሚፈራ ሲኾን፤

10 - 'Abasa (He Frowned) - 010

فَأَنتَ عَنۡهُ تَلَهَّىٰ
አንተ ከእርሱ ትዝዘናጋለህ፡፡

11 - 'Abasa (He Frowned) - 011

كَلَّآ إِنَّهَا تَذۡكِرَةٞ
ተከልከል፡፡ እርሷ ማስገንዘቢያ ናት፡፡

12 - 'Abasa (He Frowned) - 012

فَمَن شَآءَ ذَكَرَهُۥ
የሻም ሰው (ቁርኣኑን) ያስታውሰዋል፡፡

13 - 'Abasa (He Frowned) - 013

فِي صُحُفٖ مُّكَرَّمَةٖ
በተከበሩ ጽሑፎች ውስጥ ነው፡፡

14 - 'Abasa (He Frowned) - 014

مَّرۡفُوعَةٖ مُّطَهَّرَةِۭ
ከፍ በተደረገች ንጹሕ በተደረገች (ጽሑፍ ውስጥ ነው)፡፡

15 - 'Abasa (He Frowned) - 015

بِأَيۡدِي سَفَرَةٖ
በጸሐፊዎቹ (መላእክት) እጆች (ንጹሕ የተደረገች)፡፡

16 - 'Abasa (He Frowned) - 016

كِرَامِۭ بَرَرَةٖ
የተከበሩና ታዛዦች በኾኑት (ጸሐፊዎች እጆች)፡፡

17 - 'Abasa (He Frowned) - 017

قُتِلَ ٱلۡإِنسَٰنُ مَآ أَكۡفَرَهُۥ
ሰው ተረገመ፤ ምን ከሓዲ አደረገው?

18 - 'Abasa (He Frowned) - 018

مِنۡ أَيِّ شَيۡءٍ خَلَقَهُۥ
(ጌታው) በምን ነገር ፈጠረው? (አያስብምን?)

19 - 'Abasa (He Frowned) - 019

مِن نُّطۡفَةٍ خَلَقَهُۥ فَقَدَّرَهُۥ
ከፍትወት ጠብታ ፈጠረው፤ መጠነውም፡፡

20 - 'Abasa (He Frowned) - 020

ثُمَّ ٱلسَّبِيلَ يَسَّرَهُۥ
ከዚያም (መውጫ) መንገዱን አገራው፡፡

21 - 'Abasa (He Frowned) - 021

ثُمَّ أَمَاتَهُۥ فَأَقۡبَرَهُۥ
ከዚያም ገደለው፤ እንዲቀበርም አደረገው፡፡

22 - 'Abasa (He Frowned) - 022

ثُمَّ إِذَا شَآءَ أَنشَرَهُۥ
ከዚያም (ማንሳቱን) በሻ ጊዜ ያስነሳዋል፡፡

23 - 'Abasa (He Frowned) - 023

كَلَّا لَمَّا يَقۡضِ مَآ أَمَرَهُۥ
በእውነት ያንን (ጌታው) ያዘዘውን ገና አልፈጸመም፡፡

24 - 'Abasa (He Frowned) - 024

فَلۡيَنظُرِ ٱلۡإِنسَٰنُ إِلَىٰ طَعَامِهِۦٓ
ሰውም ወደ ምግቡ ይመልከት፡፡

25 - 'Abasa (He Frowned) - 025

أَنَّا صَبَبۡنَا ٱلۡمَآءَ صَبّٗا
እኛ ውሃን ማንቧቧትን ያንቧቧን መኾናችንን፡፡

26 - 'Abasa (He Frowned) - 026

ثُمَّ شَقَقۡنَا ٱلۡأَرۡضَ شَقّٗا
ከዚያም ምድርን (በደካማ ቡቃያ) መሰንጠቅን የሰነጠቅን፤

27 - 'Abasa (He Frowned) - 027

فَأَنۢبَتۡنَا فِيهَا حَبّٗا
በውስጧም እኽልን ያበቀልን፤

28 - 'Abasa (He Frowned) - 028

وَعِنَبٗا وَقَضۡبٗا
ወይንንም፤ እርጥብ (ያበቀልን)፤

29 - 'Abasa (He Frowned) - 029

وَزَيۡتُونٗا وَنَخۡلٗا
የዘይት ወይራንም ዘንባባንም፤

30 - 'Abasa (He Frowned) - 030

وَحَدَآئِقَ غُلۡبٗا
ጭፍቆች አትክልቶችንም፤

31 - 'Abasa (He Frowned) - 031

وَفَٰكِهَةٗ وَأَبّٗا
ፍራፍሬንም ገለባንም፤ (ያበቀልን መኾናችንን ይመልከት)፡፡

32 - 'Abasa (He Frowned) - 032

مَّتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ
ለእናንተም ለእንስሶቻችሁም መጠቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን ሠራን)፡፡

33 - 'Abasa (He Frowned) - 033

فَإِذَا جَآءَتِ ٱلصَّآخَّةُ
አደንቋሪይቱም (መከራ) በመጣች ጊዜ፤

34 - 'Abasa (He Frowned) - 034

يَوۡمَ يَفِرُّ ٱلۡمَرۡءُ مِنۡ أَخِيهِ
ሰው ከወንድሙ በሚሸሽበት ቀን፤

35 - 'Abasa (He Frowned) - 035

وَأُمِّهِۦ وَأَبِيهِ
ከናቱም ካባቱም፤

36 - 'Abasa (He Frowned) - 036

وَصَٰحِبَتِهِۦ وَبَنِيهِ
ከሚስቱም ከልጁም፤

37 - 'Abasa (He Frowned) - 037

لِكُلِّ ٱمۡرِيٕٖ مِّنۡهُمۡ يَوۡمَئِذٖ شَأۡنٞ يُغۡنِيهِ
ከእነርሱ ለየሰው ሁሉ በዚያ ቀን (ከሌላው) የሚያብቃቃው ኹነታ አልለው፡፡

38 - 'Abasa (He Frowned) - 038

وُجُوهٞ يَوۡمَئِذٖ مُّسۡفِرَةٞ
ፊቶች በዚያ ቀን አብሪዎች ናቸው፤

39 - 'Abasa (He Frowned) - 039

ضَاحِكَةٞ مُّسۡتَبۡشِرَةٞ
ሳቂዎችም ተደሳቾችም ናቸው፡፡

40 - 'Abasa (He Frowned) - 040

وَوُجُوهٞ يَوۡمَئِذٍ عَلَيۡهَا غَبَرَةٞ
ፊቶችም በዚያ ቀን በላያቸው ላይ ትቢያ አልለባቸው፤

41 - 'Abasa (He Frowned) - 041

تَرۡهَقُهَا قَتَرَةٌ
ጥቁረት ትሸፍናቸዋለች፤

42 - 'Abasa (He Frowned) - 042

أُوْلَـٰٓئِكَ هُمُ ٱلۡكَفَرَةُ ٱلۡفَجَرَةُ
እነዚያ እነሱ ከሓዲዎቹ አመጸኞቹ ናቸው፡፡

Scroll to Top