النازعات

 

An-Nazi'at

 

Those who drag forth

1 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 001

وَٱلنَّـٰزِعَٰتِ غَرۡقٗا
በኃይል አውጪዎች በኾኑት፤

2 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 002

وَٱلنَّـٰشِطَٰتِ نَشۡطٗا
በቀስታ መምዘዝንም መዘዦች በኾኑት፤

3 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 003

وَٱلسَّـٰبِحَٰتِ سَبۡحٗا
መዋኘትም ዋኚዎች በኾኑት፤

4 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 004

فَٱلسَّـٰبِقَٰتِ سَبۡقٗا
መቅደምንም ቀዳሚዎች በኾኑት፤

5 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 005

فَٱلۡمُدَبِّرَٰتِ أَمۡرٗا
ነገርንም አስተናባሪዎች በኾኑት (መላእክት) እምላለሁ፡፡ (በእርግጥ ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

6 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 006

يَوۡمَ تَرۡجُفُ ٱلرَّاجِفَةُ
ተርገፍጋፊይቱ (ምድር) በምትርገፈገፍበት ቀን፤

7 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 007

تَتۡبَعُهَا ٱلرَّادِفَةُ
ለጣቂይቱ የምትከተላት ስትኾን (ትቀሰቀሳላችሁ)፡፡

8 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 008

قُلُوبٞ يَوۡمَئِذٖ وَاجِفَةٌ
በዚያ ቀን ልቦች ተሸባሪዎች ናቸው፡፡

9 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 009

أَبۡصَٰرُهَا خَٰشِعَةٞ
ዓይኖቻቸው ተዋራጆች (አቀርቃሪዎች) ናቸው፡፡

10 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 010

يَقُولُونَ أَءِنَّا لَمَرۡدُودُونَ فِي ٱلۡحَافِرَةِ
«እኛ ወደ መጀመሪያይቱ ኹነታ ተመላሾች ነን?» ይላሉ፡፡

11 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 011

أَءِذَا كُنَّا عِظَٰمٗا نَّخِرَةٗ
«የበሰበሱ አጥንቶች በኾን ጊዜ (እንቀሰቀሳለን?)»

12 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 012

قَالُواْ تِلۡكَ إِذٗا كَرَّةٌ خَاسِرَةٞ
«ይህቺ ያን ጊዜ ባለ ከሳራ መመለስ ናት» ይላሉ፡፡

13 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 013

فَإِنَّمَا هِيَ زَجۡرَةٞ وَٰحِدَةٞ
እርሷም አንዲት ጩኸት ብቻ ናት፡፡

14 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 014

فَإِذَا هُم بِٱلسَّاهِرَةِ
ወዲያውኑም እነርሱ እንቅልፍ በሌለባት (ምድር) ላይ ይኾናሉ፡፡

15 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 015

هَلۡ أَتَىٰكَ حَدِيثُ مُوسَىٰٓ
የሙሳ ወሬ መጣልህን?

16 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 016

إِذۡ نَادَىٰهُ رَبُّهُۥ بِٱلۡوَادِ ٱلۡمُقَدَّسِ طُوًى
ጌታው በተቀደሰው ሸለቆ በጡዋ በጠራው ጊዜ፤

17 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 017

ٱذۡهَبۡ إِلَىٰ فِرۡعَوۡنَ إِنَّهُۥ طَغَىٰ
ወደ ፈርዖን ኺድ፡፡ እርሱ ወሰን አልፏልና፡፡

18 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 018

فَقُلۡ هَل لَّكَ إِلَىٰٓ أَن تَزَكَّىٰ
በለውም፡- «ወደ መጥራራትህ ላንተ (መንገድ) አለህን?»

19 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 019

وَأَهۡدِيَكَ إِلَىٰ رَبِّكَ فَتَخۡشَىٰ
«ወደ ጌታህም ልመራህ ትፈራውም ዘንድ፤ (መንገድ አለህን?)» አለው፡፡

20 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 020

فَأَرَىٰهُ ٱلۡأٓيَةَ ٱلۡكُبۡرَىٰ
ታላቂቱንም ተዓምር አሳየው፡፡

21 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 021

فَكَذَّبَ وَعَصَىٰ
አስተባበለም፤ አመጸም፡፡

22 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 022

ثُمَّ أَدۡبَرَ يَسۡعَىٰ
ከዚያም (ለማጥፋት) የሚተጋ ኾኖ ዞረ፡፡

23 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 023

فَحَشَرَ فَنَادَىٰ
(ሰራዊቶቹን) ሰበሰበም፤ ተጣራም፡፡

24 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 024

فَقَالَ أَنَا۠ رَبُّكُمُ ٱلۡأَعۡلَىٰ
አለም፡- «እኔ ታላቁ ጌታችሁ ነኝ፡፡»

25 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 025

فَأَخَذَهُ ٱللَّهُ نَكَالَ ٱلۡأٓخِرَةِ وَٱلۡأُولَىٰٓ
አላህም በኋለኛይቱና በፊተኛይቱ (ቃል) ቅጣት ያዘው፡፡

26 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 026

إِنَّ فِي ذَٰلِكَ لَعِبۡرَةٗ لِّمَن يَخۡشَىٰٓ
በዚህ ውስጥ ለሚፈራ ሰው በእርግጥ መገምገሚያ አለበት፡፡

27 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 027

ءَأَنتُمۡ أَشَدُّ خَلۡقًا أَمِ ٱلسَّمَآءُۚ بَنَىٰهَا
ባፈጣጠር እናንተ ይበልጥ የበረታችሁ ናችሁን? ወይንስ ሰማይ? (አላህ) ገነባት፡፡

28 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 028

رَفَعَ سَمۡكَهَا فَسَوَّىٰهَا
ከፍታዋን አጓነ፤ አስተካከላትም፡፡

29 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 029

وَأَغۡطَشَ لَيۡلَهَا وَأَخۡرَجَ ضُحَىٰهَا
ሌሊቷንም አጨለመ፡፡ ቀንዋንም ገለጸ፡፡

30 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 030

وَٱلۡأَرۡضَ بَعۡدَ ذَٰلِكَ دَحَىٰهَآ
ምድርንም ከዚህ በኋላ ዘረጋት፡፡

31 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 031

أَخۡرَجَ مِنۡهَا مَآءَهَا وَمَرۡعَىٰهَا
ውሃዋንና ግጦሿን ከእርሷ አወጣ፡፡

32 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 032

وَٱلۡجِبَالَ أَرۡسَىٰهَا
ጋራዎችንም አደላደላቸው፡፡

33 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 033

مَتَٰعٗا لَّكُمۡ وَلِأَنۡعَٰمِكُمۡ
ለእናንተና ለእንስሶቻችሁ መጣቀሚያ ይኾን ዘንድ (ይህን አደረገ)፡፡

34 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 034

فَإِذَا جَآءَتِ ٱلطَّآمَّةُ ٱلۡكُبۡرَىٰ
ታላቂቱም መዐት በመጣች ጊዜ፣

35 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 035

يَوۡمَ يَتَذَكَّرُ ٱلۡإِنسَٰنُ مَا سَعَىٰ
ሰው ሁሉ የሠራውን በሚያስታውስበት ቀን፣

36 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 036

وَبُرِّزَتِ ٱلۡجَحِيمُ لِمَن يَرَىٰ
ገሀነምም ለሚያይ ሰው በተገለጠች ጊዜ፣

37 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 037

فَأَمَّا مَن طَغَىٰ
የካደ ሰውማ፣

38 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 038

وَءَاثَرَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
ቅርቢቱንም ሕይወት የመረጠ፣

39 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 039

فَإِنَّ ٱلۡجَحِيمَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ
ገሀነም እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

40 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 040

وَأَمَّا مَنۡ خَافَ مَقَامَ رَبِّهِۦ وَنَهَى ٱلنَّفۡسَ عَنِ ٱلۡهَوَىٰ
በጌታው ፊት መቆምን የፈራ ሰውማ ነፍሱንም ከዝንባሌዋ የከለከለ

41 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 041

فَإِنَّ ٱلۡجَنَّةَ هِيَ ٱلۡمَأۡوَىٰ
ገነት እርሷ በእርግጥ መኖሪያው ናት፡፡

42 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 042

يَسۡـَٔلُونَكَ عَنِ ٱلسَّاعَةِ أَيَّانَ مُرۡسَىٰهَا
«ከሰዓቲቱ መቼ ነው መኾኛዋ?» ሲሉ ይጠይቁሃል፡፡

43 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 043

فِيمَ أَنتَ مِن ذِكۡرَىٰهَآ
አንተ እርሷን ከማስታወስ በምን ውስጥ ነህ?

44 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 044

إِلَىٰ رَبِّكَ مُنتَهَىٰهَآ
(የዕውቀት) መጨረሻዋ ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

45 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 045

إِنَّمَآ أَنتَ مُنذِرُ مَن يَخۡشَىٰهَا
አንተ የሚፈራትን ሰው አስፈራሪ ብቻ ነህ፡፡

46 - An-Nazi'at (Those who drag forth) - 046

كَأَنَّهُمۡ يَوۡمَ يَرَوۡنَهَا لَمۡ يَلۡبَثُوٓاْ إِلَّا عَشِيَّةً أَوۡ ضُحَىٰهَا
እነርሱ በሚያዩዋት ቀን ያንዲት ቀን ምሽትን ወይም ረፏዷን እንጅ ያልቆዩ ይመስላሉ፡፡

Scroll to Top