المرسلات

 

Al-Mursalat

 

The Emissaries

1 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 001

وَٱلۡمُرۡسَلَٰتِ عُرۡفٗا
ተከታታይ ኾነው በተላኩት፣

2 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 002

فَٱلۡعَٰصِفَٰتِ عَصۡفٗا
በኀይል መንፈስን ነፋሾች በኾኑትም፣

3 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 003

وَٱلنَّـٰشِرَٰتِ نَشۡرٗا
መበተንን በታኞች በኾኑትም፤ (ነፋሶች)፣

4 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 004

فَٱلۡفَٰرِقَٰتِ فَرۡقٗا
መለየትን ለይዎች በኾኑትም፣

5 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 005

فَٱلۡمُلۡقِيَٰتِ ذِكۡرًا
መገሠጫን (ወደ ነቢያት) ጣይዎች በኾኑትም፣

6 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 006

عُذۡرًا أَوۡ نُذۡرًا
ምክንያትን ለማስወገድ ወይም ለማስፈራራት (ጣይዎች በኾኑት መላእክት) እምላለሁ፡፡

7 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 007

إِنَّمَا تُوعَدُونَ لَوَٰقِعٞ
ያ የምትስፈራሩበት (ትንሣኤ) በእርግጥ ኋኝ ነው፡፡

8 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 008

فَإِذَا ٱلنُّجُومُ طُمِسَتۡ
ከዋክብትም (ብርሃንዋ) በታበሰች ጊዜ፡፡

9 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 009

وَإِذَا ٱلسَّمَآءُ فُرِجَتۡ
ሰማይም በተከፈተች ጊዜ፡፡

10 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 010

وَإِذَا ٱلۡجِبَالُ نُسِفَتۡ
ጋራዎችም በተንኮተኮቱ ጊዜ፡፡

11 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 011

وَإِذَا ٱلرُّسُلُ أُقِّتَتۡ
መልክተኞቹም ወቅት በተደረገላቸው ጊዜ፡፡

12 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 012

لِأَيِّ يَوۡمٍ أُجِّلَتۡ
ለየትኛው ቀን ተቀጠሩ (የሚባል ሲኾን)፤

13 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 013

لِيَوۡمِ ٱلۡفَصۡلِ
ለመለያው ቀን (በተባለ ጊዜ፤ በፍጡሮች መካከል ይፈረዳል)፡፡

14 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 014

وَمَآ أَدۡرَىٰكَ مَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِ
የመለያውም ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?

15 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 015

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡ {1}
{1} ይህ አንቀጽ በዚህ ምእራፍ ውስጥ 10 ግዜ ተደጋግሟል

16 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 016

أَلَمۡ نُهۡلِكِ ٱلۡأَوَّلِينَ
የፊተኞቹን (ሕዝቦች) አላጠፋንምን?

17 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 017

ثُمَّ نُتۡبِعُهُمُ ٱلۡأٓخِرِينَ
ከዚያም የኋለኞቹን እናስከትላቸዋለን፡፡

18 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 018

كَذَٰلِكَ نَفۡعَلُ بِٱلۡمُجۡرِمِينَ
በአመጸኞች ሁሉ እንደዚሁ እንሠራለን፡፡

19 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 019

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

20 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 020

أَلَمۡ نَخۡلُقكُّم مِّن مَّآءٖ مَّهِينٖ
ከደካማ ውሃ አልፈጠርናችሁምን?

21 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 021

فَجَعَلۡنَٰهُ فِي قَرَارٖ مَّكِينٍ
በተጠበቀ መርጊያ ውስጥም (በማሕፀን) አደረግነው፡፡

22 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 022

إِلَىٰ قَدَرٖ مَّعۡلُومٖ
እስከ ታወቀ ልክ ድረስ፡፡

23 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 023

فَقَدَرۡنَا فَنِعۡمَ ٱلۡقَٰدِرُونَ
መጠንነውም፤ ምን ያማርንም መጣኞች ነን!

24 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 024

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

25 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 025

أَلَمۡ نَجۡعَلِ ٱلۡأَرۡضَ كِفَاتًا
ምድርን ሰብሳቢ አላደረግናትምን?

26 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 026

أَحۡيَآءٗ وَأَمۡوَٰتٗا
ሕያዋን ኾናችሁ ሙታንም ኾናችሁ፡፡

27 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 027

وَجَعَلۡنَا فِيهَا رَوَٰسِيَ شَٰمِخَٰتٖ وَأَسۡقَيۡنَٰكُم مَّآءٗ فُرَاتٗا
በውስጧም ከፍተኛዎችን ተራራዎች አደረግን፡፡ ጣፋጭ ውሃንም አጠጣናችሁ፡፡

28 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 028

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

29 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 029

ٱنطَلِقُوٓاْ إِلَىٰ مَا كُنتُم بِهِۦ تُكَذِّبُونَ
«ወደዚያ በእርሱ ታስተባብሉ ወደ ነበራችሁት (ቅጣት) አዝግሙ፡፡

30 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 030

ٱنطَلِقُوٓاْ إِلَىٰ ظِلّٖ ذِي ثَلَٰثِ شُعَبٖ
«ባለ ሦስት ቅርንጫፎች ወደ ኾነው ጥላ አዝግሙ፤» (ይባላሉ)፡፡

31 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 031

لَّا ظَلِيلٖ وَلَا يُغۡنِي مِنَ ٱللَّهَبِ
አጠላይ ያልኾነ ከእሳቱም ላንቃ የማያድን ወደ ኾነው (አዝግሙ)፡፡

32 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 032

إِنَّهَا تَرۡمِي بِشَرَرٖ كَٱلۡقَصۡرِ
እርሷ እንደ ታላላቅ ሕንጻ የኾኑን ቃንቄዎች ትወረውራለች፡፡

33 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 033

كَأَنَّهُۥ جِمَٰلَتٞ صُفۡرٞ
(ቃንቄውም) ልክ ዳለቻዎች ግመሎችን ይመስላል፡፡

34 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 034

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

35 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 035

هَٰذَا يَوۡمُ لَا يَنطِقُونَ
ይህ የማይናገሩበት ቀን ነው፡፡

36 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 036

وَلَا يُؤۡذَنُ لَهُمۡ فَيَعۡتَذِرُونَ
ይቅርታም ይጠይቁ ዘንድ፤ ለእነርሱ አይፈቀድላቸውም፡፡

37 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 037

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

38 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 038

هَٰذَا يَوۡمُ ٱلۡفَصۡلِۖ جَمَعۡنَٰكُمۡ وَٱلۡأَوَّلِينَ
ይህ መለያው ቀን ነው፡፡ እናንተንም የፊተኞቹንም ሰብሰብናችሁ፡፡

39 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 039

فَإِن كَانَ لَكُمۡ كَيۡدٞ فَكِيدُونِ
ለናንተም (ለማምለጥ) ብልሃት እንዳላችሁ ተተናኮሉኝ፡፡

40 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 040

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ላስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

41 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 041

إِنَّ ٱلۡمُتَّقِينَ فِي ظِلَٰلٖ وَعُيُونٖ
ጥንቁቆቹ በጥላዎችና በምንጮች ውስጥ ናቸው፡፡

42 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 042

وَفَوَٰكِهَ مِمَّا يَشۡتَهُونَ
ከሚከጅሉትም ሁሉ በፍራፍሬዎች ውስጥ ናቸው፡፡

43 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 043

كُلُواْ وَٱشۡرَبُواْ هَنِيٓـَٔۢا بِمَا كُنتُمۡ تَعۡمَلُونَ
«ትሠሩት በነበራችሁት ዋጋ የምትደሰቱ ኾናችሁ ብሉ፣ ጠጡም፤» (ይባላሉ)፡፡

44 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 044

إِنَّا كَذَٰلِكَ نَجۡزِي ٱلۡمُحۡسِنِينَ
እኛ እንደዚሁ መልካም ሠሪዎችን ሁሉ እንመነዳለን፡፡

45 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 045

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

46 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 046

كُلُواْ وَتَمَتَّعُواْ قَلِيلًا إِنَّكُم مُّجۡرِمُونَ
ብሉ፤ ጥቂትንም (ጊዜ) ተጠቀሙ፡፡ እናንተ አመጸኞች ናችሁና፡፡

47 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 047

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

48 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 048

وَإِذَا قِيلَ لَهُمُ ٱرۡكَعُواْ لَا يَرۡكَعُونَ
«ለእነርሱ ስገዱም» በተባሉ ጊዜ አይሰግዱም፡፡

49 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 049

وَيۡلٞ يَوۡمَئِذٖ لِّلۡمُكَذِّبِينَ
ለአስተባባዮች በዚያ ቀን ወዮላቸው፡፡

50 - Al-Mursalat (The Emissaries) - 050

فَبِأَيِّ حَدِيثِۭ بَعۡدَهُۥ يُؤۡمِنُونَ
ከእርሱም ሌላ በየትኛው ንግግር ያምናሉ?

Scroll to Top