የአረብኛ ቋንቋ አፃፃፍና ጁዝ አመን ከቁርአን(ሙስሀፍ) ተማር በአማርኛ ቋንቋ የተዘጋጀ መፅሀፍ አዘጋጅ ዶክተር ሀይሰም ሰርሀን መፅሀፉ የአፃፃፍ ስልትን ቅጅ በማድረግ ቀስ በቀስ ፊደሎችን በተለያዩ ቅርፆቹና አገባቦቹ ከዚያም በተለያዩ አጫጭር እውቀት ተኮር የሆኑ መትኖች ላይ ተግባራዊ በማድረግ ላይ እንዴት መፃፍ እንዳለብን ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን፤ የኡስማኒ የአፃፃፍ ዘዴን (ይህም በኡስማን ኢብኑ አፋን አላህ ስራዉን ይውደድለት ዘመን ቁርአን የተፃፈበት አፃፃፍ) በጁዝ አመ ላይ ተግባራዊ በማድረግና በማስተማር ላይ አላማ አድርጓል፤ መፅሀፉ አርኪና ተናፋቂ ሲሆን ለህፃናት፣ ለአዋቂዎች፣ ለአረብኛ ቋንቋ ተናጋሪዎችና አረብኛን መናገር ለማይችሉ ተስማሚ ሆኖ ተዘጋጅቷል።