العلق

 

Al-'Alaq

 

The Clot

1 - Al-'Alaq (The Clot) - 001

ٱقۡرَأۡ بِٱسۡمِ رَبِّكَ ٱلَّذِي خَلَقَ
አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡{1}
{1} ይህ አንቀጽና ቀጥሎ ያሉት ከቁርአን መጀመሪያ የወረዱ አንቀጾች ናቸው። በኑር ተራራ ላይ በምገኘው የሂራእ ዋሻ ውስጥ ነቢዩ ሰ/ዐ/ወ/ ኸልዋ ወጥተው እያሉ ነው የወረደባቸው። (ቡኻሪና ሙስሊም፤ የወህይ አጀማመር ምእራፍ)

2 - Al-'Alaq (The Clot) - 002

خَلَقَ ٱلۡإِنسَٰنَ مِنۡ عَلَقٍ
ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡

3 - Al-'Alaq (The Clot) - 003

ٱقۡرَأۡ وَرَبُّكَ ٱلۡأَكۡرَمُ
አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤

4 - Al-'Alaq (The Clot) - 004

ٱلَّذِي عَلَّمَ بِٱلۡقَلَمِ
ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡

5 - Al-'Alaq (The Clot) - 005

عَلَّمَ ٱلۡإِنسَٰنَ مَا لَمۡ يَعۡلَمۡ
ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡

6 - Al-'Alaq (The Clot) - 006

كَلَّآ إِنَّ ٱلۡإِنسَٰنَ لَيَطۡغَىٰٓ
በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡

7 - Al-'Alaq (The Clot) - 007

أَن رَّءَاهُ ٱسۡتَغۡنَىٰٓ
ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡

8 - Al-'Alaq (The Clot) - 008

إِنَّ إِلَىٰ رَبِّكَ ٱلرُّجۡعَىٰٓ
መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡

9 - Al-'Alaq (The Clot) - 009

أَرَءَيۡتَ ٱلَّذِي يَنۡهَىٰ
አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡

10 - Al-'Alaq (The Clot) - 010

عَبۡدًا إِذَا صَلَّىٰٓ
ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤

11 - Al-'Alaq (The Clot) - 011

أَرَءَيۡتَ إِن كَانَ عَلَى ٱلۡهُدَىٰٓ
አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤

12 - Al-'Alaq (The Clot) - 012

أَوۡ أَمَرَ بِٱلتَّقۡوَىٰٓ
ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤

13 - Al-'Alaq (The Clot) - 013

أَرَءَيۡتَ إِن كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰٓ
አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤

14 - Al-'Alaq (The Clot) - 014

أَلَمۡ يَعۡلَم بِأَنَّ ٱللَّهَ يَرَىٰ
አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?

15 - Al-'Alaq (The Clot) - 015

كَلَّا لَئِن لَّمۡ يَنتَهِ لَنَسۡفَعَۢا بِٱلنَّاصِيَةِ
ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡

16 - Al-'Alaq (The Clot) - 016

نَاصِيَةٖ كَٰذِبَةٍ خَاطِئَةٖ
ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡

17 - Al-'Alaq (The Clot) - 017

فَلۡيَدۡعُ نَادِيَهُۥ
ሸንጎውንም ይጥራ፡፡

18 - Al-'Alaq (The Clot) - 018

سَنَدۡعُ ٱلزَّبَانِيَةَ
(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡

19 - Al-'Alaq (The Clot) - 019

كَلَّا لَا تُطِعۡهُ وَٱسۡجُدۡۤ وَٱقۡتَرِب۩
ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡ {1}
{1} እዚህ የንባብ ሱጁድ አለ። ይህ የመጨረሻ ሱጁድ ነው።

Scroll to Top