الليل

 

Al-Layl

 

The Night

1 - Al-Layl (The Night) - 001

وَٱلَّيۡلِ إِذَا يَغۡشَىٰ
በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡

2 - Al-Layl (The Night) - 002

وَٱلنَّهَارِ إِذَا تَجَلَّىٰ
በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡

3 - Al-Layl (The Night) - 003

وَمَا خَلَقَ ٱلذَّكَرَ وَٱلۡأُنثَىٰٓ
ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡

4 - Al-Layl (The Night) - 004

إِنَّ سَعۡيَكُمۡ لَشَتَّىٰ
ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡

5 - Al-Layl (The Night) - 005

فَأَمَّا مَنۡ أَعۡطَىٰ وَٱتَّقَىٰ
የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡

6 - Al-Layl (The Night) - 006

وَصَدَّقَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ
በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤

7 - Al-Layl (The Night) - 007

فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡيُسۡرَىٰ
ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

8 - Al-Layl (The Night) - 008

وَأَمَّا مَنۢ بَخِلَ وَٱسۡتَغۡنَىٰ
የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤

9 - Al-Layl (The Night) - 009

وَكَذَّبَ بِٱلۡحُسۡنَىٰ
በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤

10 - Al-Layl (The Night) - 010

فَسَنُيَسِّرُهُۥ لِلۡعُسۡرَىٰ
ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡

11 - Al-Layl (The Night) - 011

وَمَا يُغۡنِي عَنۡهُ مَالُهُۥٓ إِذَا تَرَدَّىٰٓ
በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡

12 - Al-Layl (The Night) - 012

إِنَّ عَلَيۡنَا لَلۡهُدَىٰ
ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡

13 - Al-Layl (The Night) - 013

وَإِنَّ لَنَا لَلۡأٓخِرَةَ وَٱلۡأُولَىٰ
መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡

14 - Al-Layl (The Night) - 014

فَأَنذَرۡتُكُمۡ نَارٗا تَلَظَّىٰ
የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡

15 - Al-Layl (The Night) - 015

لَا يَصۡلَىٰهَآ إِلَّا ٱلۡأَشۡقَى
ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡

16 - Al-Layl (The Night) - 016

ٱلَّذِي كَذَّبَ وَتَوَلَّىٰ
ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡

17 - Al-Layl (The Night) - 017

وَسَيُجَنَّبُهَا ٱلۡأَتۡقَى
አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡

18 - Al-Layl (The Night) - 018

ٱلَّذِي يُؤۡتِي مَالَهُۥ يَتَزَكَّىٰ
ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡

19 - Al-Layl (The Night) - 019

وَمَا لِأَحَدٍ عِندَهُۥ مِن نِّعۡمَةٖ تُجۡزَىٰٓ
ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡

20 - Al-Layl (The Night) - 020

إِلَّا ٱبۡتِغَآءَ وَجۡهِ رَبِّهِ ٱلۡأَعۡلَىٰ
ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡

21 - Al-Layl (The Night) - 021

وَلَسَوۡفَ يَرۡضَىٰ
ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡

Scroll to Top