الأعلى

 

Al-A'la

 

The Most High

1 - Al-A'la (The Most High) - 001

سَبِّحِ ٱسۡمَ رَبِّكَ ٱلۡأَعۡلَى
ከሁሉ በላይ የኾነውን ጌታህን ስም አሞግሥ፡፡

2 - Al-A'la (The Most High) - 002

ٱلَّذِي خَلَقَ فَسَوَّىٰ
የዚያን (ሁሉን ነገር) የፈጠረውን ያስተካከለውንም፡፡

3 - Al-A'la (The Most High) - 003

وَٱلَّذِي قَدَّرَ فَهَدَىٰ
የዚያንም የወሰነውን፡፡ (ለተፈጠረለት ነገር) የመራውንም፡፡

4 - Al-A'la (The Most High) - 004

وَٱلَّذِيٓ أَخۡرَجَ ٱلۡمَرۡعَىٰ
የዚያንም ግጦሽን (ለምለም አድርጎ) ያወጣውን፡፡

5 - Al-A'la (The Most High) - 005

فَجَعَلَهُۥ غُثَآءً أَحۡوَىٰ
(ከዚያ) ደረቅ ጥቁር ያደረገውንም (አምላክ ስም አሞግስ)፡፡

6 - Al-A'la (The Most High) - 006

سَنُقۡرِئُكَ فَلَا تَنسَىٰٓ
(ቁርኣንን) በእርግጥ እናስነብብሃለን፤ አትረሳምም፡፡

7 - Al-A'la (The Most High) - 007

إِلَّا مَا شَآءَ ٱللَّهُۚ إِنَّهُۥ يَعۡلَمُ ٱلۡجَهۡرَ وَمَا يَخۡفَىٰ
አላህ ከሻው ነገር በስተቀር፡፡ እርሱ ግልጹን የሚሸሸገውንም ሁሉ ያውቃልና፡፡

8 - Al-A'la (The Most High) - 008

وَنُيَسِّرُكَ لِلۡيُسۡرَىٰ
ለገሪቱም (ሕግጋት) እንገጥምሃለን፡፡

9 - Al-A'la (The Most High) - 009

فَذَكِّرۡ إِن نَّفَعَتِ ٱلذِّكۡرَىٰ
ግሣጼይቱ ብትጠቅም (ሰዎችን) ገሥጽም፡፡

10 - Al-A'la (The Most High) - 010

سَيَذَّكَّرُ مَن يَخۡشَىٰ
(አላህን) የሚፈራ ሰው በእርግጥ ይገሠጻል፡፡

11 - Al-A'la (The Most High) - 011

وَيَتَجَنَّبُهَا ٱلۡأَشۡقَى
መናጢውም ይርቃታል፡፡

12 - Al-A'la (The Most High) - 012

ٱلَّذِي يَصۡلَى ٱلنَّارَ ٱلۡكُبۡرَىٰ
ያ ታላቂቱን እሳት የሚገባው፡፡

13 - Al-A'la (The Most High) - 013

ثُمَّ لَا يَمُوتُ فِيهَا وَلَا يَحۡيَىٰ
ከዚያም በእርሷ ውስጥ አይሞትም ሕያውም አይኾንም፡፡

14 - Al-A'la (The Most High) - 014

قَدۡ أَفۡلَحَ مَن تَزَكَّىٰ
የተጥራራ ሰው በእርግጥ ዳነ፡፡

15 - Al-A'la (The Most High) - 015

وَذَكَرَ ٱسۡمَ رَبِّهِۦ فَصَلَّىٰ
የጌታውንም ስም ያወሳና የሰገደ፡፡

16 - Al-A'la (The Most High) - 016

بَلۡ تُؤۡثِرُونَ ٱلۡحَيَوٰةَ ٱلدُّنۡيَا
ይልቁንም ቅርቢቱን ሕይወት ትመርጣላችሁ፡፡

17 - Al-A'la (The Most High) - 017

وَٱلۡأٓخِرَةُ خَيۡرٞ وَأَبۡقَىٰٓ
መጨረሻይቱ (ሕይወት) በላጭ ሁል ጊዜ ዘውታሪም ስትኾን፡፡

18 - Al-A'la (The Most High) - 018

إِنَّ هَٰذَا لَفِي ٱلصُّحُفِ ٱلۡأُولَىٰ
ይህ በፊተኞቹ መጻሕፍት ውስጥ ያልለ ነው፡፡

19 - Al-A'la (The Most High) - 019

صُحُفِ إِبۡرَٰهِيمَ وَمُوسَىٰ
በኢብራሂምና በሙሳ ጽሑፎች ውስጥ፡፡

Scroll to Top